🔇Unmute
ጎንደር ፤ መጋቢት 2/2018 (ኢዜአ)፦ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የሴቶችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነትን በማሳደግ ፖለቲካዊ ተሳትፏቸውን ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚናን እንደሚጫወት ተገለፀ።
በኢትዮጵያ 30 ሚሊዮን ሴቶችን የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ለማድረግ ያለመ ንቅናቄ ተጀመረ
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ቀኑ ቢያድጉ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ አካል የሆነውን ፋይዳ የዲጂታል መታወቂያን ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ ነው።

በዚህም በዞኑ 280 ሺህ ሴቶች ፋይዳ የዲጂታል መታወቂያን በማውጣት ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።፡
ፋይዳ መታወቂያ ሴቶች የፋይናንስና ሌሎች የመንግስት አገልግሎቶችን በዲጂታል አሰራር በተቀላጠፈ መንገድ እንዲያገኙ በማድረግ ጊዜን፣ ጉልበትንና እንግልትን መቀነሱን አስረድተዋል።
በተለይም በገጠሩ ክፍል የሚገኙ ሴቶች በመሬት ነክ ጉዳዮች ላይ ይገጥማቸው የነበረውን የፍትህ እጦት ለማስተካከል ያስቻለ መሆኑንም አመልክተዋል።
በዞኑ የምእራብ ደንቢያ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ ሰናይት ማሩ ፤ ፋይዳ የዲጂታል መታወቂያ በመንግስት ተቋማት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለማግኘት እንድችል አግዞኛል ብለዋል፡፡
በጎንደር ዙሪያ ወረዳ የማክሰኚት ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ ብርቱካን ማንደፍሮ በበኩላቸው፤ ፋይዳ የዲጂታል መታወቂያ እኔንና ቤተሰቤን የጤና መድህን ተጠቃሚ በማድረግ ቀልጣፋ አገልግሎት እንድናገኝ ምቹ ሁኔታን ፈጥሮልናል ብለዋል።
በዞኑ በዘንድሮ ዓመት 725 ሺህ ሴቶችን የፋይዳ መታወቂያ ተጠቃሚ ለማድረግ ግብ መያዙን ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025