የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ የግብርና ምርምር ውጤቶች ለተጠቃሚው በመድረሳቸው በዘርፉ ተጨባጭ ውጤት እየመጣ ነው

Mar 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሆሳእና፤ መጋቢት 1/2018(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የግብርና ምርምር ውጤቶች ለተጠቃሚው በመድረሳቸው በዘርፉ ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ፡፡

የክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዓመታዊ የምርምር ሥራዎች ግምገማ መድረክ ዛሬ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል።


በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የግብርናና ገጠር ልማት ክላስተር አስተባበሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ሀላፊ ኡስማን ሱሩር በዚህ ወቅት እንደገለጹት፣ በክልሉ ምርታማነትን የሚያሳድጉ የምርምር ሥራዎች ለተጠቃሚው በመድረሳቸው በግብርናው ዘርፍ ተጨባጭ ለውጥ እየመጣ ነው፡፡

የግብርና ምርምር ተቋማት አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅ፣ ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ ዝርያዎችን በማላመድና ዘመናዊ የእርሻ አስተዳደር ዘዴዎችን በማስተዋወቅ የዘርፉን ምርታማነት እያሳደጉ ነው ብለዋል፡፡

በተለይም በሽታና ድርቅን ተቋቁመው የተሻለ ምርት የሚሰጡ ዝርያዎችን፣ የቅመማቅመም ምርቶች እንዲሁም አትክልትና ፍራፍሬዎችን ለአርሶ አደሮች የማቅረብ ሥራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ግብርናን በማዘመን ኢኮኖሚያዊ መዋቅራዊ ሽግግርን ከግብ ለማድረስ ተመራማሪዎች አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ማፍለቅ፣ ማባዛትና ማሰራጨት ላይ ተግተው ሊሰሩ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።


የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፀጋዬ ተረፈ በበኩላቸው የአየር ንብረት ለውጥን ተቋቁመው የተሻለ ምርት በሚሰጡ ዝርያዎች ላይ ምርምር እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የምርምር ውጤቶች ለአርሶ አደሮች ደርሰው በተጨባጭ ማሳ ላይ እንዲተገበሩ ከዩኒቨርሲቲዎች እና ከሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ጋር በቅርበት እየሰራን ነው ብለዋል።

በተያዘው በጀት ዓመትም ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድጉ የምርምር ውጤቶችን ለአርሶ አድሩና ለተጠቃሚዎች ተደራሽ መደረጋቸውን ገልጸዋል።

ከዛሬ ጀምሮ ለሦስት ቀናት በሚቆየው መድረክ ከተለያዩ ተቋማት የቀረቡ ከ265 በላይ የምርምር ሥራዎች እንደሚገመገሙ ተመላክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025