የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ የግብርና አቅምን በመለየት የተከናወኑ የአሰራር ማሻሻያዎች ውጤት አምጥተዋል

Mar 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ዲላ ፤ መጋቢት 1/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የግብርና አቅምን በጥናት በመለየት የተከናወኑ የአሰራር ማሻሻያዎች እና በቴክኖሎጂ የተደገፉ ትግበራዎች ውጤት ማምጣታቸውን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለጸ።

በክልሉ የግብርና ምርምር ውጤቶች ለተጠቃሚው በመድረሳቸው በዘርፉ ተጨባጭ ውጤት እየመጣ ነው

የክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት "በምርምር የታገዘ ግብርና፣ የበለፀገ ማኅበረሰብ፣ የማይበገር ኢኮኖሚ መገንባት" በሚል መሪ ቃል ያዘጋጀው አውደ ጥናት በዲላ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።


በአውደ ጥናቱ በሰብል፣ በእንስሳትና በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ እንዲሁም በተለያዩ ዘርፎች የተሰሩ 1 ሺህ 107 የምርምር ሥራዎች ቀርበው የሚገመገሙ መሆኑ ተመላክቷል።

በወቅቱም በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ በክልሉ የግብርና ሽግግርን ለማፋጠን ጥናትና ምርምርን መሠረት ያደረጉ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ ነው።

በተለይም የክልሉን የግብርና አቅም በመለየት የተከናወኑ የአሠራር ማሻሻያዎችና በቴክኖሎጂ የተደገፉ ትግበራዎች ውጤት ማምጣታቸውን ጠቁመዋል።

ለዚህም በክልሉ በሩዝ ልማት የተመዘገበውን ውጤት ለአብነት በመጥቀስ፣ መሰል ውጤታማ የምርምር ሥራዎች መጠናከር እንዳለባቸው አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የሰብል ምርምር ዳይሬክተር ፍቃዱ ግርማ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የግብርና ምርምርን ከሀገራዊ የልማት ኢኒሼቲቮች ጋር በማጣጣም በተከናወኑ ተግባራት ስኬት መገኘቱን ገልጸዋል።


በተለይም በአረንጓዴ አሻራ፣ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት እንዲሁም በሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮች ግብርናውን ለማሻገር የሚያስችሉ ተጨማሪ አቅሞችን መፍጠር መቻሉን ተናግረዋል።

ግብርናው ለተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች አጋዥ ኃይል ሆኖ በመውጣት ሽግግሩን እንዲመራም እየተከናወኑ ያሉ የምርምር ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ገልጸዋል።

የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በዞኑ በቡናና በእንሰት ልማት ላይ የታየው ለውጥ በሰብሎቹ ላይ የተካሄዱ የምርምር ሥራዎች ውጤታማ በመሆናቸው የመጣ ነው ብለዋል።


በተለይም በቡና ልማት ረገድ በምርምር ግኝቶች ላይ ተመስርተው የወጡ የተሻሻሉ ዝርያዎች፣ በሄክታር በአማካይ 5 ኩንታል የነበረውን የቡና ምርት ወደ 11 ኩንታል ማሳደጉን አስረድተዋል።

ይሁን እንጂ የአፈር አሲዳማነት ዛሬም የዞኑ የግብርና ልማት ማነቆ መሆኑን በመጥቀስ፣ በዚህ ረገድ የሚከናወኑ የምርምር ሥራዎች መጠናከር እንዳለባቸው አሳስበዋል።

የአውደ ጥናቱ ዓላማ የተቀናጁ የምርምር ሥራዎችን በማውጣት የተሻለ የግብርና ልማትን ማረጋገጥ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አብዮት መብራቴ (ዶ/ር) ናቸው።


ኢንስቲትዩቱ የተለያዩ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅ የግብርና ምርታማነትን እያገዘ መሆኑን ገልጸው፤ በተያዘው ዓመት በ470 ሄክታር የአርሶ አደር ማሳ ላይ ሰርቶ በማሳየት የተሻሻሉ ቴክኖሎጂዎችን ከማስተዋወቅ ባለፈ፣ የምርጥ ዘር አቅርቦትን በራስ አቅም ለመሸፈን የሚያስችል አቅም መፈጠሩን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025