የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በከተማ ግብርና የተከናወኑ ውጤታማ ተግባራት በምርት አቅርቦት ላይ ተጨባጭ ለውጥ እያመጡ ነው  

Mar 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 1/2018(ኢዜአ)፦በከተማ ግብርና ዘርፍ የተከናወኑ ውጤታማ ተግባራት በምርት አቅርቦት ላይ ተጨባጭ ለውጥ እያመጡ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር አባይ ገለጹ።

በኦሮሚያ ክልል የእንስሳት ሀብት ልማትን ለማዘመን የተቀረፁ ኢንሼቲቮች ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገቡ ነው

በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ለ975 አንቀሳቃሾች ዶሮ፣ የዶሮ ኬጅ እና የመኖ ድጋፍ ተደረጓል።


‎‎የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር አባይ እንደገለጹት፤ የከተማ ግብርናን በሁሉም ክፍለ ከተሞች በማስፋፋትና የምርት አቅርቦትን በማሳደግ የኑሮ ውድነትን ለመቀነስና የገበያ መረጋጋትን ለመፍጠር በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።

‎‎እስካሁን በተከናወኑ ተግባራትም በአቅርቦት ረገድ አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን አስታውቀዋል።

‎‎ይህ ውጤት ሊገኝ የቻለው በሁሉም አካላት የተቀናጀ ርብርብ መሆኑን የጠቆሙት ምክትል ከንቲባው፤ በቀጣይም ዘርፉን ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ በትጋት መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።


‎ጠንክሮ በመስራት ከራስ ፍጆታ ባለፈ ለማህበረሰቡ የሚሆን ምርት ማምረት እንደሚቻል ጠቅሰው የከተማ አስተዳደሩ ለዘርፉ መጠናከርና ለተሳታፊዎች ማበረታቻ የሚሆኑ ስራዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

‎‎የዛሬው የድጋፉ ተጠቃሚዎችም በዘርፉ ጠንክረው በመስራት ከራስ ፍጆታ ባሻገር ማማረት እንደሚገባቸው ጠቁመዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ የአርሶ አደርና ከተማ ግብርና ልማት ኮሚሽን ኮሚሽነር ባዩ ሽጉጤ በበኩላቸው፤ ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን በላይ ነዋሪዎች በከተማ ግብርና በቀጥታ ተጠቃሚ መሆናቸውን አመልክተዋል።


‎የከተማ ግብርና መርሃግብር ዜጎችን ከሸማችነት ወደ አምራችነት እንዲሻገሩ በማስቻል ከራሳቸው አልፈው ለሌሎች የሚተርፉ ማድረጉ የዘርፉን ስኬት የሚያሳይ መሆኑን ጠቁመዋል።

‎መርሐ ግብሩ በከተማ ደረጃ የግብርና ስራ መስራትና ውጤታማ መሆን እንደሚቻል በተግባር ያረጋገጠ መሆኑን ተናግረዋል።

‎የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ ምስክር ነጋሽ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በክፍለ ከተማው ነዋሪዎችን በከተማ ግብርና ተጠቃሚ የሚያደርጉ ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።


‎የድጋፉ ተጠቃሚዎች በበኩላቸው፤ የተደረገላቸውን ድጋፍ በአግባቡ በመጠቀም ከራሳቸው ፍጆታ አልፈው ምርታቸውን ለሌሎች ተደራሽ ለማድረግ በትጋት እንደሚሰሩ አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025