የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በከተማ ግብርና የተከናወኑ ውጤታማ ተግባራት በምርት አቅርቦት ላይ ተጨባጭ ለውጥ እያመጡ ነው  

Mar 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 1/2018(ኢዜአ)፦በከተማ ግብርና ዘርፍ የተከናወኑ ውጤታማ ተግባራት በምርት አቅርቦት ላይ ተጨባጭ ለውጥ እያመጡ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር አባይ ገለጹ።

በኦሮሚያ ክልል የእንስሳት ሀብት ልማትን ለማዘመን የተቀረፁ ኢንሼቲቮች ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገቡ ነው

በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ለ975 አንቀሳቃሾች ዶሮ፣ የዶሮ ኬጅ እና የመኖ ድጋፍ ተደረጓል።


‎‎የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር አባይ እንደገለጹት፤ የከተማ ግብርናን በሁሉም ክፍለ ከተሞች በማስፋፋትና የምርት አቅርቦትን በማሳደግ የኑሮ ውድነትን ለመቀነስና የገበያ መረጋጋትን ለመፍጠር በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።

‎‎እስካሁን በተከናወኑ ተግባራትም በአቅርቦት ረገድ አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን አስታውቀዋል።

‎‎ይህ ውጤት ሊገኝ የቻለው በሁሉም አካላት የተቀናጀ ርብርብ መሆኑን የጠቆሙት ምክትል ከንቲባው፤ በቀጣይም ዘርፉን ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ በትጋት መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።


‎ጠንክሮ በመስራት ከራስ ፍጆታ ባለፈ ለማህበረሰቡ የሚሆን ምርት ማምረት እንደሚቻል ጠቅሰው የከተማ አስተዳደሩ ለዘርፉ መጠናከርና ለተሳታፊዎች ማበረታቻ የሚሆኑ ስራዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

‎‎የዛሬው የድጋፉ ተጠቃሚዎችም በዘርፉ ጠንክረው በመስራት ከራስ ፍጆታ ባሻገር ማማረት እንደሚገባቸው ጠቁመዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ የአርሶ አደርና ከተማ ግብርና ልማት ኮሚሽን ኮሚሽነር ባዩ ሽጉጤ በበኩላቸው፤ ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን በላይ ነዋሪዎች በከተማ ግብርና በቀጥታ ተጠቃሚ መሆናቸውን አመልክተዋል።


‎የከተማ ግብርና መርሃግብር ዜጎችን ከሸማችነት ወደ አምራችነት እንዲሻገሩ በማስቻል ከራሳቸው አልፈው ለሌሎች የሚተርፉ ማድረጉ የዘርፉን ስኬት የሚያሳይ መሆኑን ጠቁመዋል።

‎መርሐ ግብሩ በከተማ ደረጃ የግብርና ስራ መስራትና ውጤታማ መሆን እንደሚቻል በተግባር ያረጋገጠ መሆኑን ተናግረዋል።

‎የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ ምስክር ነጋሽ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በክፍለ ከተማው ነዋሪዎችን በከተማ ግብርና ተጠቃሚ የሚያደርጉ ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።


‎የድጋፉ ተጠቃሚዎች በበኩላቸው፤ የተደረገላቸውን ድጋፍ በአግባቡ በመጠቀም ከራሳቸው ፍጆታ አልፈው ምርታቸውን ለሌሎች ተደራሽ ለማድረግ በትጋት እንደሚሰሩ አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026