የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልል ከተሞች እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ጽዱ እና ምቹ ከተሞችን እየፈጠረ ነው

Mar 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ መጋቢት 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች የሚገኙ ከተሞችን ለነዋሪዎች ምቹ፣ ፅዱ እና የቱሪዝም መስህብ ለማድረግ የሚያስችሉ የኮሪደር ልማት ሥራዎች በስፋት እየተከናወኑ መሆኑ ተገለጸ።

የኮሪደር እና መልሶ ማልማት አነስተኛ ቢዝነሶችን ይበልጥ ዘመናዊ፣ ለስራ እና ለሸማቹ ሳቢ በሆነ መንገድ መልሶ በመገንባት የተሰራ ነው

ከልማቱ ጎን ለጎንም የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያስችል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመዘርጋት ስራም እየተከናወነ መሆኑ ተመላክቷል።

የሲዳማ ክልል ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ብሩክ ሰለሞን ለኢዜአ እንደገለጹት፤ መንግሥት ከተሞች የብልጽግና ማሳያ እንዲሆኑ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት የክልሉ ከተሞች ትርጉም ባለው መልኩ እንዲለሙ ትኩረት ተሰጥቷል።


በሀዋሳ ከተማ የተጀመረውን ውጤታማ የኮሪደር ልማት ስራ በክልሉ በሚገኙ ሌሎች ከተሞች ለማስፋፋት ታቅዶ ውጤታማ ስራ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

በአሁኑ ወቅት በከንቲባ በሚመሩ ይርጋለም፣ በንሣ ዳዬ፣ አለታ ወንዶ፣ ወንዶ ገነት፣ ለኩ እና አለታ ጭኮ ከተሞች በፌዴራልና በክልል መንግሥት በጀት ልማቱ እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል።

በተጨማሪም ሀገረ ሰላም፣ ጠጢቻ፣ ቦና እና መጪሻን ጨምሮ ከ60 በላይ አነስተኛ ከተሞች በአቅማቸው ልክ ወደ ኮሪደር ልማት ሥራ መግባታቸውን ተናግረዋል።

የኮሪደር ልማቱ የአስፓልት መንገዶች፣ ስማርት የኤሌክትሪክ ፖሎች፣ ምቹ የእግረኛና የብስክሌት መንገዶች፣ የመዝናኛ ፓርኮች እና አረንጓዴ ስፍራዎችን ያካተተ መሆኑንም ጠቅሰዋል።

አቶ ብሩክ አክለውም፣ በሀዋሳ ከተማ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ወደ ስድስት ተጨማሪ ከተሞች ለማስፋፋት የህንጻ ግንባታ መጀመሩን አስታውቀዋል።


በተመሳሳይ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሙራድ ከድር በበኩላቸው፤ ወልቂጤ አንጋፋ የንግድ ኮሪደር ብትሆንም ከቆይታዋ አንጻር ሳትለማ መቆየቷን ጠቅሰው፣ አሁን ላይ ግን ከተማዋን ለማዘመን 25 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን ገልጸዋል።

በእስካሁኑ ሂደት 7 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ መከናወኑን ጠቅሰው ይህም የእግረኛ መንገዶችን የማስዋብ፣ ስማርት ፖል፣ የብስክሌት መንገድ እና የሕፃናት መዝናኛዎችን ያካተተ ነው ብለዋል።

ሁለተኛው ምዕራፍ 15 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ለማካሄድ የዲዛይን ሥራ ተጠናቆ ተቋራጭ የመለየት ሂደት ላይ መደረሱንም አመልክተዋል።

ይህ ልማት ከተማዋን ለኢንቨስትመንትና ለቱሪዝም ተመራጭ ከማድረጉ ባለፈ ለበርካታ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠሩን ከንቲባው ገልጸዋል።

በተጨማሪም አገልግሎትን ዲጂታላይዝ ለማድረግና የተገልጋዩን እርካታ ለማሳደግ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ግንባታ ለመጀመር የቦታ ልየታ መጠናቀቁን አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026