🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 13/2018 (ኢዜአ)፦ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በአማራ ክልል የልማት ሥራዎችን ለመመልከት ባህርዳር ገብተዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባህርዳር ደጃዝማች በላይ ዘለቀ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድርና ካቢኔያቸው፣ የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር አመራሮች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እንዲሁም የባህርዳር ከተማ ነዋሪዎች ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው የተፈጥሮ ገጸ በረከት፣ የሰላምና የውበት ተምሳሌት በሆነችው፣ ታሪክን ከለመለመ ተፈጥሮ ጋር አዛምዶ በያዘው ጣና ሐይቅና በግርማዊው ዓባይ ወንዝ በታጀበችው ውቧ ባሕር ዳር ከተማ ገብተናል ብለዋል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድርና ካቢኔያቸው፣ የባህርዳር ከተማ አመራሮች ላደረጉላቸው ደማቅ አቀባበልም አመስግነዋል።

በምርቃታቸውና በጸሎታቸው ላልተለዩን የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እንዲሁም እንግዳን በፈገግታና በፍቅር መቀበል ለጋስ ማንነቱ ለሆነው የባሕር ዳር ከተማ ሕዝብ ከልብ የመነጨ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ ሲሉም በመልዕክታቸው ጠቅሰዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በባህርዳር ቆይታቸው የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው ይመለከታሉ።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026