የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በጋምቤላ ክልል በግብርና፣ በማዕድንና በሌሎች የልማት ዘርፎች ውጤታማ ስራዎች ተከናውነዋል

Mar 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጋምቤላ፤ መጋቢት 14/2018 (ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በግብርና በማዕድንና በሌሎች የልማት ዘርፎች ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ ገለፁ።

‎የክልሉ ምክር ቤት ዛሬ ባካሔደው መደበኛ ጉባኤ የክልሉን የግማሽ በጀት ዓመት የልማትና የመልካም አስተዳደር እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት አድምጧል።

‎ርዕሰ መስተዳድሯ የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርቱን ለምክር ቤቱ ባቀረቡበት ወቅት እንዳሉት በክልሉ በሰላም ግንባታ፣ በግብርና፣ በማዕድን፣ በገቢና በሌሎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ውጤታማ ስራዎች ተከናውነዋል ብለዋል።

‎በክልሉ ተከስቶ የነበረውን የፀጥታ ችግር ለመፍታት በሕዝቡና በፀጥታ አካሉ የተደረገው የተቀናጀት ጥረት የተረጋጋ ሰላም ማምጣት አስችሏል ነው ያሉት።

‎‎‎በ2017/18 የምርት ዘመን ከ186 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በማልማት ከ6 ነጥብ 2 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰብ መቻሉንም ገልፀዋል።

ይህም ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ኩንታል ብልጫ እንዳለው በሪፖርቱ አመላክተዋል።

‎‎በማዕድን ልማት ዘርፉም በመጀመሪዎቹ ስድስት ወራት 3 ሺህ ኪሎ ግራም ወርቅ ወደ ብሔራዊ ባንክ ለማስገባት ታቅዶ 3 ሺህ 860 ኪሎ ግራም መግባቱን ጠቅሰዋል።

‎አፈፃፀሙ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ1 ሺህ 057 ኪሎ ግራም ብልጫ እንዳለው ነው የገለጹት።

‎‎የክልሉን የገቢ አቅም ለማሳደግ በተከናወኑ ተግባራትም በግማሽ ዓመቱ ከ2 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በላይ መሰብሰቡን በሪፖርቱ አመላክቷል።

በተጨማሪም በትምህርት፣ በጤና፣ በንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት፣ በመሠረተ ልማት ዝርጋታ፣ በስራ ዕድል ፈጠራና በሌሎች የልማት መስኮች አበረታች ስራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026