🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 15/2018 (ኢዜአ)፡- የኮሪደር ልማቱ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ፣ ከባቢያዊ እና ሌሎችም በርካታ ትሩፋቶች ማበርከቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከተማ፣ ከተሜነት፣ ክትመትና የኮሪደር ልማት በተሰኙ ጉዳዮች ላይ ከቃና ቲቪ ጋር ቆይታ አድርገዋል።
በዚሁ ወቅትም፤ የኮሪደር ልማቱ በኢኮኖሚ፣ በሥራ ፈጠራ፣ በክኅሎት፣ በከባቢያዊ ፋይዳ፣ ዓየር ንብረት ጥበቃ እና በማኅበራዊ ግብ ረገድ በርካታ ትሩፋቶች ማበርከቱን አብራርተዋል።
ሥራ አጥነት በማክሮ ኢኮኖሚው አንዱ ስብራት ተብሎ መቀመጡን አውስተው፤ የኮሪደር ልማት እየተሠራም ፕሮጀክቱ ካለቀ በኋላም የሥራ ዕድል መፍጠሩን አስረድተዋል።
በክኅሎት ረገድም የኮሪደር ልማት በርካታ ባለሙያዎች ማፍራቱን ጠቁመው፤ እነዚህ ወጣቶች ዲዛይን ሠርተው የሚያከናውኑት ግንባታ የሚያስደንቅ ነው ብለዋል።
የኮሪደር ልማቱን ተከትሎ በርካታ ቤቶችን በመላ ሀገሪቱ በአጭር ጊዜ ገንብተን እያጠናቀቅን ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እነዚህ ቤቶች የኮሪደር ልማቱ አካል መሆናቸውን አስታውቀዋል።
የኮሪደር ልማቱ የነበረውን የመንገድ መዘጋጋት በመቀነስ የጉዞ ጊዜን ማሳጠር ማስቻሉ ሌላኛው ትሩፋቱ መሆኑን አስገንዝበዋል።
በቱሪዝም ረገድም ከፍተኛ አስተዋጽዖ ማበርከቱን ጠቅሰው፤ ዘንድሮ ካለፈው ዓመት የበለጠ የቱሪዝም እንቅስቃሴ መኖሩን ጠቅሰዋል።
ንጽህናው የተጠበቀ፣ ያማረ ዘላቂ ሥነ-ምኅዳር መፍጠር በማደግ ላይ ያሉ ሀገራት ህልም መሆኑን ያደጉትም ያን የመጠበቅ ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸው፤ ስለዚህ ከከባቢያዊ ግብ አኳያ የኮሪደር ልማት ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል ብለዋል።
በንጹህ ከባቢ መኖር በገንዘብ የማንለካቸውን የጤና ትሩፋቶች ያስገኛል፤ ለዓየር ንብረት ጥበቃም ከፍተኛ አስተዋጽዖ አለው ሲሉ አብራርተዋል።
የኮሪደር ልማት ሥራ ሂደቱ ከባድ ውጤቱ ጥሩ መሆኑን በመግለጽ፤ ኮሪደርን ሰዎች ስም ሊያወጡለት ሲሞክሩ መጀመሪያ ግቦቹን ማየት እና ግቦቹን በምን ደረጃ እንዳሳካ ማረጋገጥ እንደሚጠበቅባቸው አመላክተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025