የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ኢትዮጵያን የቀጣናው ተመራጭ የኢንቨስትመንት መዳረሻ አድርጓታል

Mar 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፡-ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው የውጭ ቀጥታ ኢንቨስተመንት ፍሰትን በማሳደግ ኢትዮጵያን የቀጣናው ተመራጭ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ማድረጉን የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ገለጹ።

"ኢንቨስት በኢትዮጵያ" ፎረም "ኢትዮጵያ ለቢዝነስ ዝግጁ ናት" በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ነው።

የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀዳሚ ተመራጭ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ሆናለች።


መንግሥት ተቋማዊ አደረጃጀቱን በመከታተልና ቴክኖሎጂ በማዘመን ለአልሚዎች የተሻለ አሰራር መዘርጋቱን ገልጸዋል።

የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለግሉ ዘርፍ ዕድገት ልዩ ትኩረት በመስጠት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ፍሰት እንዲጨምር ማድረጉን ገልጸዋል።

በማክሮ ኢኮኖሚው መረጋጋት በመፈጠሩ የዋጋ ግሽበት ቀንሷል፣ የውጭ ምንዛሪ ክምችትም አድጓል ነው ያሉት።

በኢትዮጵያ የታክስ አስተዳደር ስርዓቱ በዲጂታል ቴክኖሎጂ መደገፉንና ዘመናዊ መሆኑን ጠቅሰው፤ የተሳለጠ የመንግስት አገልግሎት እየተሰጠ ስለመሆኑ አብራርተዋል።

በዚህም ኢትዮጵያ ዓለም አቀፋዊና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትስስሯን በማሳደግ የቀጣናው መሪ የኢኮኖሚ ማዕከል ሆናለች ብለዋል።


ኢትዮጵያ ጠንካራ ኢኮኖሚ፣ ሰፊ የህዝብ ቁጥር ያላትና አዳዲስ የኢንቨስትመንት ዕድሎች የሚፈጠሩባት ሀገር ናት ያሉት የገንዘብ ሚኒስትሩ፤ የባንክ ስርዓቱም እንዲዘምን መደረጉን ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ የአየር መንገድ ግንባታ፣ በቤቶች ልማት እና በሌሎችም ዘርፎች ምቹ የኢንቨስትመንት አማራጮች እንዳሉ ገልጸው፤ ኢትዮጵያ ለኢንቨስትመንት በሯ ክፍት ነው ብለዋል።

በኢትዮጵያ ምቹ የኢንቨስትመንት ዕድሎች እንዳሉ ጠቅሰው፤ የልማት አጋሮች በኢትዮጵያ በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች መሰማራት እንደሚችሉ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025