🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ ንግድና ኢንቨስትመንት ዝግጁ የሆነች፣ የዕምቅ ዐቅሞችና የዕድሎች መሶብ ናት ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአዲስ አበባ አራተኛውን "Invest in Ethiopia 2026" የቢዝነስ ፎረምን ዛሬ በይፋ አስጀምረዋል።
ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ ንግድና ኢንቨስትመንት ዝግጁ የሆነች፣ የዕምቅ ዐቅሞችና የዕድሎች መሶብ ናት ብለዋል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት።

ኢትዮጵያ የጥንታዊ ሥልጣኔ ባለቤት ብቻ አይደለችም፤ ዛሬ በፈጣን የለውጥ ጎዳና ላይ ያለች፣ ግዙፍና ተወዳዳሪ ኢኮኖሚ እየገነባች የምትገኝ ሰፊና አዋጭ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ናት ብለዋል።
የኢንቨስትመንት መሶባችን በትጉኅና ወጣት ሕዝብ ዐቅም፣ ባልተነካ የተፈጥሮ ጸጋ እና በስትራቴጂያዊ መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ የታደለ መሆኑን አመልክተዋል።
በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርማችንና በተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያችን ለዘመናዊና ተወዳዳሪ ኢኮኖሚ የማይመቹ አሠራሮችን በቆራጥነት በመቀየር እንደ ፋይናንስና ቴሌኮም ያሉ ቁልፍ ዘርፎችን ለዓለም አቀፍ ኢንቨስትመንት ክፍት መደረጋቸውን ነው ያወሱት።
የመሠረተ ልማት አውታር መስፋፋቱ የሕዳሴ ግድብ ተጠናቆ አስተማማኝ የኃይል ምንጭ መፈጠሩ ኢትዮጵያ ለኢንቨስትመንት ያላትን ምቹ ምኅዳርና ቁርጠኝነት ለዓለም የሚያረጋግጡ ታላላቅ ማሳያዎች እንደሆኑም ተናግረዋል።
እኛ የምንፈልገው ድጋፍ ሳይሆን አጋርነትን ነው፤ ርዳታን ሳይሆን ኢንቨስትመንትን ነው ያሉት አቶ ተመስገን፤ ለባለ ሀብቶች ምቹ፣ ግልጽና ተራማጅ የሆነ የሕግ ማሕቀፍ አዘጋጅተናልም ብለዋል።
መንግስት የኢትዮጵያ ብልጽግና የሚረጋገጠው በግሉ ዘርፍ ንቁ ተሳትፎ፣ በፈጠራና በርትዕ በሚመራ የኢኮኖሚ ምኅዳር መሆኑን በጽኑ እንደሚያምን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ካፒታል፣ ለችሎታ እና ለዕድል በሯን ወለል አድርጋ መክፈቷንም አመልክተዋል።
የዛሬው መድረክም ራዕይን ከተግባር፣ ዕቅድና መሻትን ደግሞ ከኢንቨስትመንት ጋር በማገናኘት የጋራ ብልጽግናችንን የምንቀርጽበት ወሳኝ ምዕራፍ ነው ሲሉም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ አሁን በፍጥነት ወደ ከፍታ እየገሠገሠች ባለችበት በዚህ ታሪካዊ የዕድገት ጉዞ፣ ለዓለም አቀፍና ለሀገር ውስጥ ባለ ሀብቶች ኢትዮጵያ ለእናንተ ዝግጁ የሆነ፣ በዕድሎችና በስኬቶች የተሞላ ታላቅ የኢንቨስትመንት መሶብ አላት፤ ኑ አብረን እንሥራ! ሲሉም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥሪ አቅርበዋል።
በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...
Sep 14, 2026
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026