የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በሸገር ከተማ ዘመናዊ የከተማ አስተዳደር ስርዓትን በመተግበር የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ትኩረት ተሰጥቷል

Mar 31, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2018(ኢዜአ)፦ ዘመናዊ የከተማ አስተዳደር ስርዓትን በመተግበር የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የሸገር ከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር) ገለጹ።

በከተማው የአርሶ አደሮች መሠረታዊ የኑሮ ማሻሻያ ሁኔታ ላይ ያተኮረ ወርክሾፕ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ተካሂዷል።


ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር) በመድረኩ እንደገለጹት፤ ባለፉት ሦስት ዓመታት ጥናትን መሠረት በማድረግ የሸገር ከተማን ለማሳደግና ለማዘመን የተለያዩ ተግባራት ሲከናወኑ ቆይተዋል።

በቴክኖሎጂ የታገዙ ተግባራትን በማከናወን የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገትን ለማስመዝገብ ትኩረት እንደተሰጠው ጠቁመው፤ ከተማው ከተመሰረተ ጀምሮ ዘመናዊ ፕላንን ጨምሮ ከተማዋን የማዘመን ስራዎች ስኬታማ እየሆኑ መምጣታቸውን አብራርተዋል።

በተለይም የከተማውን አርሶ አደር የአኗኗር ዘይቤ በማሻሸል በኩል ወርክሾፑ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህም በእቅድና በአፈፃፀም መካከል ያለውን ክፍተት ለማጥበብ፣ ልማቱን በተጨባጭ መረጃ ለመመዘንና የተገኘውን ለውጥ ለማስቀጠል ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ተናግረዋል።

በአጠቃላይ ዘመናዊ የከተማ አስተዳደር ስርዓትን በመተግባር የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።


የሸገር ከተማ አስተዳደር ፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ አህመድ ቶፊቅ በበኩላቸው፤ ከተማው አርሶ አደሩን ማዕከል ባደረገ አዲስ እሳቤ የተመሰረተ መሆኑን ተናግረዋል።

የአርሶ አደሩን ሕይወት ለመለወጥና ተጠቃሚነቱን ለማሳደግ ጥናቶች እየተከናወኑ መሆኑንም ጠቅሰዋል።

ከተማውንና አርሶ አደሩን በማቀራረብ የነበረውን የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር ስብራት ለመጠገን እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው፤ አርሶ አደሮችን ከእርሻ ስራ ወደ ኢንዱስትሪ፣ የእንስሳት እርባታ፣ ንግድና አገልግሎት ዘርፎች ለማሸጋገር በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።


በወርክሾፑ ጥናታዊ ጽሁፍ ያቀረቡት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የምግብ ዋስትና ዘርፍ ተመራማሪ መስከረም አቢ፤ ከተሜነት የኢኮኖሚ እድገትን በማፋጠን በኩል ከፍተኛ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።

የአርሶ አደሩን ሕይወት ለማሻሻል እንደ ትምህርትና ጤና ያሉ መሠረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ምርትና ምርታማነትን መጨመር እና የቁጠባ ባህልን ማሳደግ ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የአርሶ አደሮችን ተጠቃሚነትና የከተማዋን እድገት አመዛዝኖ ማስኬድ ለከተማዋ ዘላቂ ስኬት ወሳኝ መሆኑን ምክረ ሀሳብ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025