የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በሸገር ከተማ ዘመናዊ የከተማ አስተዳደር ስርዓትን በመተግበር የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ትኩረት ተሰጥቷል

Mar 31, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2018(ኢዜአ)፦ ዘመናዊ የከተማ አስተዳደር ስርዓትን በመተግበር የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የሸገር ከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር) ገለጹ።

በከተማው የአርሶ አደሮች መሠረታዊ የኑሮ ማሻሻያ ሁኔታ ላይ ያተኮረ ወርክሾፕ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ተካሂዷል።


ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር) በመድረኩ እንደገለጹት፤ ባለፉት ሦስት ዓመታት ጥናትን መሠረት በማድረግ የሸገር ከተማን ለማሳደግና ለማዘመን የተለያዩ ተግባራት ሲከናወኑ ቆይተዋል።

በቴክኖሎጂ የታገዙ ተግባራትን በማከናወን የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገትን ለማስመዝገብ ትኩረት እንደተሰጠው ጠቁመው፤ ከተማው ከተመሰረተ ጀምሮ ዘመናዊ ፕላንን ጨምሮ ከተማዋን የማዘመን ስራዎች ስኬታማ እየሆኑ መምጣታቸውን አብራርተዋል።

በተለይም የከተማውን አርሶ አደር የአኗኗር ዘይቤ በማሻሸል በኩል ወርክሾፑ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህም በእቅድና በአፈፃፀም መካከል ያለውን ክፍተት ለማጥበብ፣ ልማቱን በተጨባጭ መረጃ ለመመዘንና የተገኘውን ለውጥ ለማስቀጠል ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ተናግረዋል።

በአጠቃላይ ዘመናዊ የከተማ አስተዳደር ስርዓትን በመተግባር የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።


የሸገር ከተማ አስተዳደር ፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ አህመድ ቶፊቅ በበኩላቸው፤ ከተማው አርሶ አደሩን ማዕከል ባደረገ አዲስ እሳቤ የተመሰረተ መሆኑን ተናግረዋል።

የአርሶ አደሩን ሕይወት ለመለወጥና ተጠቃሚነቱን ለማሳደግ ጥናቶች እየተከናወኑ መሆኑንም ጠቅሰዋል።

ከተማውንና አርሶ አደሩን በማቀራረብ የነበረውን የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር ስብራት ለመጠገን እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው፤ አርሶ አደሮችን ከእርሻ ስራ ወደ ኢንዱስትሪ፣ የእንስሳት እርባታ፣ ንግድና አገልግሎት ዘርፎች ለማሸጋገር በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።


በወርክሾፑ ጥናታዊ ጽሁፍ ያቀረቡት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የምግብ ዋስትና ዘርፍ ተመራማሪ መስከረም አቢ፤ ከተሜነት የኢኮኖሚ እድገትን በማፋጠን በኩል ከፍተኛ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።

የአርሶ አደሩን ሕይወት ለማሻሻል እንደ ትምህርትና ጤና ያሉ መሠረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ምርትና ምርታማነትን መጨመር እና የቁጠባ ባህልን ማሳደግ ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የአርሶ አደሮችን ተጠቃሚነትና የከተማዋን እድገት አመዛዝኖ ማስኬድ ለከተማዋ ዘላቂ ስኬት ወሳኝ መሆኑን ምክረ ሀሳብ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026