የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የቻይና የፋይናንስ ተቋማት ለኢትዮጵያ የልማትና ኢኮኖሚ ማሻሻያ ድጋፍ ማድረጋቸውን እንደሚቀጥሉ አረጋገጡ

Mar 31, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ የቻይና የፋይናንስ ተቋማት ለኢትዮጵያ የልማትና የኢኮኖሚ ማሻሻያ ስራዎች የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታወቁ።

በገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ የተመራ ከፍተኛ የኢትዮጵያ ልዑክ በቻይና የስራ ጉብኝት እያደረገ ነው።

ልዑኩ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር)፣ የገንዘብ ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችን ያካተተ ነው።

በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈራ ደርበውም የተገኙ ሲሆን፤ የልዑኩ ጉብኝት ሁለት አላማዎችን ያነገበ ነው።

ይህም በሂደት ላይ ያለውን የዕዳ ሽግሽግ ድርድር ማጠናቀቅ እና ለቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት ግንባታ የሚውል የፋይናንስ ስምምነቶችን ማፋጠን ላይ ትኩረቱን አድርጓል።

ኢትዮጵያ ከቻይና ጋር ያላትን የቆየ የኢኮኖሚ አጋርነትም ይበልጥ እንደሚያጠናከር ተመላክቷል።

ልዑካን ቡድኑ በቆይታው ከቻይና ኤክስፖርት-ኢምፖርት ባንክ፣ ከቻይና ኢንዱስትሪና ንግድ ባንክ እና ከቻይና ልማት ባንክ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ተከታታይ ውይይቶችን አድርጓል።

ውይይቶቹ የዕዳ ሽግሽግ ሂደቱን በማጠናቀቅና ለኢትዮጵያ ቅድሚያ ለሚሰጣቸው የመሠረተ ልማት ኢንቨስትመንቶች አዲስ የፋይናንስ ምንጭ ለማግኘት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ናቸው።

የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ በዕዳ ሽግሽግ ድርድሩ ላይ ከፍተኛ መሻሻል መታየቱን ገልጸው፤ ሂደቱ አሁን ላይ የማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ መድረሱን አመልክተዋል።

ይህ ሂደት በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቅ ለመንግስት አስፈላጊውን የበጀት ነፃነት በመፍጠር፣ ሀገራዊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎችንና ዕድገት ተኮር የልማት ተግባራትን ለማፋጠን እንደሚያስችል ተናግረዋል።

የቻይና የፋይናንስ ተቋማት በበኩላቸው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አመራር ኢትዮጵያ እያስመዘገበች ያለውን የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ውጤቶች አድንቀዋል።

መንግስት በዕዳ ሽግሽግ ሂደቱ ላይ እያሳየ ያለውን ገንቢ ተሳትፎና የተመዘገበውን ስኬት በማድነቅ፣ ለኢትዮጵያ የልማትና የኢኮኖሚ ማሻሻያ ጥረት የሚያደርጉትን ድጋፍ እንደሚቀጥሉ በድጋሚ አረጋግጠዋል።

በተጨማሪም ሚኒስትሩ የኢትዮጵያና የቻይናን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ጥንካሬ በማንሳት፣ የፋይናንስ ተቋማቱ ለቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ የሚውለውን የፋይናንስ ማዕቀፍ የመገምገምና የማጽደቅ ሂደት እንዲያፋጥኑ ጥሪ አቅርበዋል።

ፕሮጀክቱ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ፋይዳና አዋጭነት ያለው መሆኑን የጠቀሱት ሚኒስትሩ፣ ይህም ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላትን የአቪዬሽን ማዕከልነት ለማጠናከርና ለረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ሽግግር ቁልፍ ሚና እንዳለው አብራርተዋል።

ሁለቱ ወገኖች በመሠረተ ልማት ፋይናንስና ኢኮኖሚ አጋርነት ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከርም ተስማምተዋል።

ይህም በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን የቆየና የጋራ ተጠቃሚነትን መሠረት ያደረገ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግር የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026