የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ሚኒስቴሩ በጋሞ ዞን ያስገነባውን የጸሀይ ኃይል ማመንጫ ለአገልግሎት አበቃ

Mar 31, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አርባ ምንጭ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በጋሞ ዞን ጋርዳ ማርታ ወረዳ በ500 ሚሊዮን ብር ወጪ ያስገነባው የጸሀይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ለአገልግሎት አበቃ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታው ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ(ዶ/ር) በምረቃው ላይ እንደገለጹት፤ ፕሮጀክቱ 710 ኪሎ ዋት ኃይል ማመንጨት የሚችል ሲሆን፣ 6 ሺህ 500 አባወራዎችን ተጠቃሚ ያደርጋል።

ፕሮጀክቱ የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እንደሚያሳልጥ ጠቅሰው፤ በተለይ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ከመፍጠር አኳያ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል።

ለፕሮጀክቱ ማስፈጸሚያ ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ መደረጉን የተናገሩት ሚኒስትር ዴኤታው፣ የአካባቢው ማህበረሰብ ለተገነባው መሠረተ ልማት ተገቢውን ጥበቃ እንዲያደርግም አሳስበዋል።

ለአካባቢው ማህበረሰብ የኃይል ስርጭቱን ለማዳረስ 7 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን መካከለኛ መስመር እንዲሁም 17 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ዝቅተኛ መስመር ተዘርግቷል ብለዋል።

ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ ብርሃን፣ በነፋስና በሌሎች የታዳሽ ኃይል ምንጮች ወደ 150 ጊጋ ዋት ማመንጨት የሚያስችል አቅም ያላት ቢሆንም፤ እስካሁን ጥቅም ላይ የዋለው 9 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ብቻ መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታው ጠቁመዋል።

የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምስ አድማሱ (ዶ/ር)፤ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በጋርዳ ማርታ ወረዳ ህዝብን ተጠቃሚ ያደረገ ፕሮጀክት ገንብቶ በማስረከቡ ምስጋና አቅርበዋል።

አካባቢው ከመሠረተ ልማት ርቆ በመቆየቱ ህዝቡ የኃይል ተጠቃሚ ሳይሆን መቆየቱን አስታውሰው፤ ፕሮጀክቱ መንግስት የገባውን ቃል በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል።

በተለይ የጤና ተቋማት የላቦራቶሪ አገልግሎት እንዲሰጡ እንዲሁም የትምህርት ተቋማት ቴክኖሎጂን እንዲጠቀሙ በማስቻል ረገድ ፕሮጀክቱ ጉልህ ፋይዳ እንዳለውም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025