የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የኢትዮጵያ ብዝኅ የኢኮኖሚ ሥርዓት የማዕድን ሃብት የዕድገት ምሰሶ የሚሆንበትን ወሳኝ ዕድል ፈጥሯል

Apr 1, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብዝኅ የኢኮኖሚ ሥርዓት የማዕድን ሃብት የዕድገት ምሰሶ የሚሆንበትን ወሳኝ ዕድል መፍጠሩን የዘርፉ ምሁራን ገለጹ።

የዘርፉ ምሁራን ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ የኢትዮጵያ የማዕድን ሃብት ልማት የዘርፉን ምርታማነት በማነቃቃት ብዝኅ የተፈጥሮ ጸጋን ወደ ጥቅም መለወጥ እያስቻለ ስኬት እያስገኘ ነው።

በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የጂኦሎጂና ማዕድን ምህንድስና ትምህርት ክፍል መምህር ግርማ ወልደትንሳኤ(ዶ/ር)፤ ሀገራዊ ለውጡ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሃብቷን የምትጠቀምበት ዕድል ፈጥሯል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ብዝኅ የኢኮኖሚ ሥርዓትም የማዕድን ሃብት ልማት የአሰራር ውስንነቶችን በመቅረፍ አስቻይ የተፈጥሮ ሃብት ንግድና ኢንቨስትመንት የምርታማነት ምኅዳር መፍጠሩን ገልጸዋል።

የተፈጥሮ ጸጋዎች በሀገር ዕድገት ገንቢ ሚና የሚወጡበት አስቻይ ሁኔታ መፈጠሩም የማዕድን ሃብቶችን በመለየት ተገቢውን የአስተዳደር ሥርዓት መፍጠር እንዳስቻለ ተናግረዋል።

የማዕድን ሀብት ለሀገር ዕድገት የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ለማሳደግ የዘርፉን ንግድና ኢንቨስትመንት ውጤታማነት የሚያስጠብቅ የጥናትና ምርምር ስራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባም መክረዋል።

በተለይም የማዕድን ጸጋዎችን የዕሴት ሰንሰለት ለማሻሻል በሚደረገው ጥረት የአካባቢ ደኅንነትና ዘላቂነትን በማስጠበቅ የዘርፉ ተዋናዮች በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።


በማዕድን ዘርፍ ኢንቨስትመንት የአርዲኮ የግል ካምፓኒ ሥራ አስኪያጅ ወዳጄ አበበ(ዶ/ር)፤ በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሽግግር ውስጥ የማዕድን ዘርፍ የድርሻውን የሚያበረክትበት ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ብዝኅ የኢኮኖሚ ሥርዓትና የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያም ለማዕድን የኢንቨስትመንት ምርታማነት ወሳኝ ዕድል መፍጠራቸውን ገልጸዋል።

ለዚህም ውጤታማ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን በማፍለቅ በተፈጥሮ ጸጋዎች የተፈጠረውን የምርታማነት መነቃቃት የበለጠ ማጠናከር እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል።

በቀጣይም የማዕድን ሃብት ምርታማነትን ለማስቀጠል በዘርፉ የተካነ የሰው ሃይልና ቴክኖሎጂ ማፍለቅ እንደሚገባ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025