🔇Unmute
ሀዋሳ፤መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ) ፡-የመካከለኛው ምስራቅ ወቅታዊ ሁኔታ በነዳጅ አቅርቦት ላይ የፈጠረውን ችግር ለመቋቋም የተቀመጡ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን በአግባቡ ልንተገብር ይገባል ሲሉ ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ።
የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በኢትዮጵያ የነዳጅ ግብይትና አቅርቦት ላይ ሊያደርስ የሚችለውን ተጽዕኖ እንዲሁም መንግሥት የሚከተላቸውን የመፍትሄ አቅጣጫዎች በተመለከተ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ሰፊ ማብራሪያ መስጠታቸው ይታወቃል።
በተለይም ነዳጅን በቁጠባ መጠቀም፣ የታዳሽ ኃይል አማራጮችን የመጠቀም ልምድ፣ የእግር ጉዞ ባህልን ማጎልበት፣ የሕዝብ ትራንስፖርትን መጠቀም፣ በነዳጅ ግብይት ላይ የሚስተዋሉ ሕገ-ወጥ ተግባራትን ማጋለጥ እና ሌሎችም ከህብረተሰቡ የሚጠበቁ ዋና ዋና ተግባራት መሆናቸውን ሚኒስትሩ አብራርተዋል።

በዚህም መሰረት የችግሩን ሁኔታ ታሳቢ ያደረገና መፍትሄዎችን ያገናዘበ አሰራር መከተልና መፍትሄውን ተግባራዊ ማድረግ አስፈላጊ ሆኗል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ የኢዜአ ሪፖርተር በሀዋሳ ከተማ ተዘዋውሮ ያነጋገራቸው የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች፤ በነዳጅ አቅርቦት ላይ የተፈጠረውን ችግር ለመቋቋም የተቀመጡ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን በአግባቡ ልንተገብር ይገባል ብለዋል።
ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል አቶ ሃይለየሱስ ወልደሰንበት፤ በመካከለኛው ምስራቅ የተከሰተው ጦርነት በነዳጅና ሌሎችም ከውጭ ሊገቡ በሚችሉ ምርቶች ላይ እጥረት መፈጠሩ የሚጠበቅ ነው ብለዋል።
እንደ ሀገር መፍትሄዎቹ ላይ በማተኮር በመተሳሰብና በመተጋገዝ ጭምር ችግሩን ልናልፈው ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።
በተለይም በነዳጅ አቅርቦት ላይ የተፈጠረውን ችግር ለመቋቋም የተቀመጡ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን በአግባቡ ልንተገብር ይገባል ብለዋል።
"እኔ ከ30 ዓመታት በላይ ብስክሌት የማሽከርከር ልምድ አለኝ" ያሉት አቶ ሃይለየሱስ፤ መሰል የትራንስፖርት አማራጮችን መጠቀምና በእግርም የመጓዝ ልምድን እናዳብር ሲሉ ተናግረዋል።፡
ሌላኛው የከተማዋ ነዋሪ አቶ መሳይ ጨርቆስ፤ የመካከለኛውን ምስራቅ ጦርነት ተከትሎ በነዳጅ አቅርቦት ላይ እጥረት መፍጠሩ ሁላችንንም ያሳሰበን በመሆኑ ችግሩን ለማለፍ መፍትሄው ላይ በትብብር መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል።
ለተፈጠረው ወቅታዊ ችግር የተቀመጡ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን መተግበር፣ መተሳሰብና ለአማራጭ መፍትሄዎች መትጋት ያስፈልጋል ሲሉ ተናግረዋል።
አቶ ቢንያም አበበ በበኩላቸው፤ የነዳጅ አቅርቦት እጥረቱ የሚያስከትለውን ጫና ለመቀነስ መንግስት ያስቀመጣቸው የመፍትሄ አማራጮች ተገቢ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በመሆኑም ለተግባራዊነቱ የመንግስት አካላት ቁጥጥር እንዳለ ሆኖ ሁላችንም እንደ ዜጋ የመፍትሄው አካል መሆን ይጠበቅብናል ብለዋል።
በሀዋሳ ታክሲ በማሽከርከር የሚተዳደሩት አቶ ደመላሽ ሞቲ፤ የነዳጅ እጥረቱ ለሁሉም ፈተና ሆኖ የመጣ ችግር ቢሆንም መፍትሄው ላይ ማተኮር የግድ ይለናል ሲሉ ተናግረዋል።
በመሆኑም እጥረቱን ለመቋቋም በመንግስት የተቀመጡ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን በአግባቡ ልንተገብር ይገባል ብለዋል።
በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...
Sep 14, 2026
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026