🔇Unmute
አክሱም ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ በአክሱም ከተማ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የተሰማሩ ወጣቶች ለፋሲካ በዓል የዶሮና እንቁላል ምርቶችን ለገበያ ለማቅረብ መዘጋጀታቸውን ገለጹ።
በአክሱም ከተማ በርካታ ወጣቶች በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በመሳተፍ ስኬታማ እየሆኑ ይገኛሉ።
በተለይም በዶሮ አርባታ ላይ የተሰማሩ ወጣቶች ለበዓል ገበያ እንቁላልና ዶሮዎችን ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ እየሆኑ ነው።
በዚሁም መሰረት በትግራይ ክልል አክሱም ከተማ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ዶሮዎችን ለፋሲካ የበዓል ገበያ ለማቅረብ ዝግጅታቸውን ማጠናቀቃቸውን ኢዜአ ያነጋገራቸው ወጣቶች ገልጸዋል።
በዘርፉ ልማት ከተሰማሩት ወጣቶች መካከል በረከት ግደይ፤ ለፋሲካ በርከት ያሉ ዶሮዎችና እንቁላል በተመጣጣኝ ዋጋ ለገበያ ለማቅረብ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ተናግሯል።

ከብድርና ቁጠባ ተቋም በተገኘ ብድር እና ከቤተሰብ ድጋፍ ተደርጎለት እርባታውን መጀመሩን የሚገልጸው በረከት በአጭር ጊዜ ስኬታማ መሆኑን ይናገራል።
በ2 ሺህ 500 ጫጩቶች ስራ መጀመሩን አስታውሶ አሁን ላይ በየእለቱ እንቁላል ለገበያ በማቅረብ ገቢ እያገኘ መሆኑን ገልፆ ለፋሲካ በአል ደግሞ የእርድ ዶሮዎችን ጨምሮ እንቁላል በልዩ ሁኔታ ለገበያ ለማቅረብ መዘጋጀቱን ተናግሯል።
ሌላኛው ወጣት ገብረመድህን ተኽሉ፤ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ተሰማርቶ በዶሮ እርባታ ስራ እራሱንና ቤተሰቡን እያገዘ መሆኑን ገልጿል።

ለፋሲካ በዓል በርከት ያሉ ዶሮዎችንና እንቁላል በተመጣጣኝ ዋጋ ለገበያ ለማቅረብ ዝግጅት ማድረጉን አንስቶ በዚህም እራሱን ተጠቃሚ ከማድረግ ባለፈ ለማህበረሰቡ ጥሩ አቅርቦት የሚሰጥ መሆኑን ነው የገለጸው።
በአክሱም ከተማ የግብርና ባለሙያ የሆኑት አቶ ሙሉ ገብረህይወት፣ በከተማዋ በሌማት ትሩፋት የተሰማሩ በርካታ ወጣቶች ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የወጣቶቹ የልማት ጥረት ከራሳቸው አልፎ ለሌሎች የስራ እድል በመፍጠርና የአካባቢው ማህበረሰብ በምርቶች ተጠቃሚ እንዲሆን እያስቻሉ ይገኛሉ ብለዋል።
በዚህም መሰረት በከተማዋ በሌማት ትሩፋት የተሰማሩ ወጣቶች በተለይም የዶሮ እና እንቁላል እንዲሁም ሌሎች ተዋጽኦዎችን ለማቅረብ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025