የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የተመዘገቡ ስኬቶች ከአሥር ዓመቱ የልማት ዕቅድ ጋር የተጣጣሙ ናቸው

Apr 8, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦በተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የተመዘገቡ ስኬቶች በሁለተኛው የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም የታቀዱና ከአሥር ዓመቱ የልማት ዕቅድ ጋር የተጣጣሙ መሆናቸውን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ገለጹ።

የገንዘብ ሚኒስቴር ባለፉት 18 ወራት የተከናወኑ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ እና መዋቅራዊ ማሻሻያዎችን ውጤታማነት የሚገመግም ዝርዝር ሪፖርት ይፋ አድርጓል።


ሪፖርቱ በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረገው የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚያዊ ማሻሻያ በተለይም የዋጋ ግሽበትን በመቀነስ፣የወጪ ንግድን በማሳደግ እንዲሁም በመንግሥት ገቢ አሰባሰብ ላይ ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገቡ ተመላክቷል።

የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ባደረጉት ንግግር፤ሪፖርቱ የገንዘብ ሚኒስቴር፣ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፣ የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን፣ የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት እና ዓለም አቀፍ አጋሮች በጋራ ያከናወኑት የሥራ ውጤት መሆኑን ገልጸዋል።

ተቋማዊ ቅንጅቱ ለተመዘገበው ስኬት ትልቅ አስተዋጽኦ ማድረጉን ጠቁመዋል።

በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የተመዘገቡት ስኬቶች በሁለተኛው የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም የታቀዱና ከአሥር ዓመቱ የልማት ዕቅድ ጋር የተጣጣሙ ናቸው ብለዋል።

ኢትዮጵያ ባለፉት ስምንት ዓመታት በግብርና፣ በኢንዱስትሪ እና የአገልግሎት ዘርፎችን ጨምሮ በሌሎችም ጠንካራና ሰፊ መሠረት ያለው የኢኮኖሚ ዕድገት በማስመዝገብ ላይ እንደምትገኝ ነው የገለጹት።

ይህም የሪፎርም ፕሮግራሙ ያለመው የመዋቅራዊ ሽግግር ነጸብራቅ መሆኑን ጠቁመዋል።


ባለፉት 18 ወራት ለዕድገት ዋና ምንጭ ተብለው በተለዩት አምስት የኢኮኖሚ ምሰሶዎች በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በማዕድን፣ በቱሪዝም እና በአይሲቲ ዘርፎች ስኬታማ ውጤቶች መመዝገባቸውን አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በሪፎርሙ የታሰበለትን ውጤት እያሳካ መሆኑንና የተከናወኑ ተግባራትም ለዚህ ማሳያ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ይህ ስኬታማ የሪፎርም ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል።

ሪፖርቱ ያለፈውን ተግባር ለመገምገም ብቻ ሳይሆን የተሻለ ዕቅድ፣ የተሻለ ቅንጅት እና የተሻለ ውጤት የሚመዘገብበትን የወደፊት ጉዞ ለመቅረጽ መሠረት የሚጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።

መረጃ ለተሻለ አስተዳደር መሠረት መሆኑን ጠቅሰው፥ የተጀመረው የፖሊሲ ቅንጅት እና የመረጃ መሠረተ ልማት ግንባታ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025