🔇Unmute
ሐረር ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በሐረር ከተማ ለትንሳኤ በዓል የሚያስፈልጉ የግብርና ምርቶች የአቅርቦት እጥረት እንዳይፈጠር የሚያስችሉ ተግባራት መከናወናቸውን የክልሉ ንግድ ልማት ኤጀንሲ ገለጸ።
ለበዓሉ የሚያስፈልጉ የግብርና ምርት አቅርቦት በበቂ ሁኔታ መኖሩንም ሻጭና ሸማቾች ተናግረዋል።
የሐረሪ ክልል ንግድ ልማት ኤጀንሲ ሃላፊ አቶ ሸሪፍ ሙሜ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ለበዓሉ የሚያስፈልጉ ምርቶች እጥረት እንዳይከሰት ከሁሉም የንግዱ ማህበረሰብ ጋር ውይይት ተደርጓል።
የምርት አቅርቦትን ከማሳለጥ አንጻርም ከክልሉ ገጠር ወረዳዎች የሚመረተውን ምርት ወደ ከተማው የማቅረብና ከተለያዩ አቅራቢዎች ጋር ትስስር በመፍጠር ምርት ወደ ከተማው እንዲገባ መደረጉን ተናግረዋል።
እንዲሁም የምስራቅ እዝ ያመረተውን ምርት ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲዳረስ ለሸማቾች ማህበራት እያቀረበ መሆኑንም አመልክተዋል።
በተጨማሪም በከተማው የቅዳሜ እና እሁድ ገበያ ስፍራዎችን የማጠናከር ስራ መስራቱን ጠቁመዋል።
ከዚሁ ጎን ለጎን ያልተገባ ዋጋ የሚጨምሩ ነጋዴዎችን የመከታተልና የመቆጣጠር ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመው በአሁኑ ወቅት ለበዓሉ የሚያስፈልጉ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ግብይት እየተፈጸመ መሆኑን አመልክተዋል።
በከተማው በተለምዶ ሞቢል በተባለው የቅዳሜና እሁድ ገበያ በአትክልት ሽያጭ የተሰማሩት ወይዘሮ በቀለች ንጉሴ ከአካባቢውና ከሌሎች ስፍራ አትክልት ለተጠቃሚው እያቀረቡ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ምርቱን በተመጣጣኝ ዋጋ በመሸጥ ህዝቡ በዓሉን በደስታ እንዲያሳልፍ ጥረት እያደረጉ እንደሚገኙ ገልጸዋል።
የበዓል ገበያ የምርት አቅርቦቱ የተሻለ መሆኑንና የክልሉ ንግድ ጽህፈት ቤት ባወጣው ዋጋ መሰረት ለተጠቃሚው በተመጣጣኝ ዋጋ እየሸጡ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የግብርና ምርት ነጋዴ የሆኑት ኢሳያስ አለማየሁ ናቸው።

ለትንሳኤ በዓል አትክልት፣ እንቁላልና ሌሎችም ምርቶች አቅርቦት መኖሩን የተናገሩት ደግሞ በስፍራው አትክልት በመሸመት ላይ የነበሩት ወይዘሮ ሃይማኖት የሺጥላ ናቸው።

ለበዓሉም የሚያስፈልገውን በአቅማቸው እየሸመቱ እንደሚገኙ የጠቀሱት ወይዘሮ ሃይማኖት ያልተገባ ዋጋ በሚጨምሩ ነጋዴዎች ላይ የሚደረገው ቁጥጥር መጠናከር እንዳለበት አመልክተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025