🔇Unmute
ሐረር ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በሐረር ከተማ ለትንሳኤ በዓል የሚያስፈልጉ የግብርና ምርቶች የአቅርቦት እጥረት እንዳይፈጠር የሚያስችሉ ተግባራት መከናወናቸውን የክልሉ ንግድ ልማት ኤጀንሲ ገለጸ።
ለበዓሉ የሚያስፈልጉ የግብርና ምርት አቅርቦት በበቂ ሁኔታ መኖሩንም ሻጭና ሸማቾች ተናግረዋል።
የሐረሪ ክልል ንግድ ልማት ኤጀንሲ ሃላፊ አቶ ሸሪፍ ሙሜ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ለበዓሉ የሚያስፈልጉ ምርቶች እጥረት እንዳይከሰት ከሁሉም የንግዱ ማህበረሰብ ጋር ውይይት ተደርጓል።
የምርት አቅርቦትን ከማሳለጥ አንጻርም ከክልሉ ገጠር ወረዳዎች የሚመረተውን ምርት ወደ ከተማው የማቅረብና ከተለያዩ አቅራቢዎች ጋር ትስስር በመፍጠር ምርት ወደ ከተማው እንዲገባ መደረጉን ተናግረዋል።
እንዲሁም የምስራቅ እዝ ያመረተውን ምርት ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲዳረስ ለሸማቾች ማህበራት እያቀረበ መሆኑንም አመልክተዋል።
በተጨማሪም በከተማው የቅዳሜ እና እሁድ ገበያ ስፍራዎችን የማጠናከር ስራ መስራቱን ጠቁመዋል።
ከዚሁ ጎን ለጎን ያልተገባ ዋጋ የሚጨምሩ ነጋዴዎችን የመከታተልና የመቆጣጠር ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመው በአሁኑ ወቅት ለበዓሉ የሚያስፈልጉ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ግብይት እየተፈጸመ መሆኑን አመልክተዋል።
በከተማው በተለምዶ ሞቢል በተባለው የቅዳሜና እሁድ ገበያ በአትክልት ሽያጭ የተሰማሩት ወይዘሮ በቀለች ንጉሴ ከአካባቢውና ከሌሎች ስፍራ አትክልት ለተጠቃሚው እያቀረቡ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ምርቱን በተመጣጣኝ ዋጋ በመሸጥ ህዝቡ በዓሉን በደስታ እንዲያሳልፍ ጥረት እያደረጉ እንደሚገኙ ገልጸዋል።
የበዓል ገበያ የምርት አቅርቦቱ የተሻለ መሆኑንና የክልሉ ንግድ ጽህፈት ቤት ባወጣው ዋጋ መሰረት ለተጠቃሚው በተመጣጣኝ ዋጋ እየሸጡ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የግብርና ምርት ነጋዴ የሆኑት ኢሳያስ አለማየሁ ናቸው።

ለትንሳኤ በዓል አትክልት፣ እንቁላልና ሌሎችም ምርቶች አቅርቦት መኖሩን የተናገሩት ደግሞ በስፍራው አትክልት በመሸመት ላይ የነበሩት ወይዘሮ ሃይማኖት የሺጥላ ናቸው።

ለበዓሉም የሚያስፈልገውን በአቅማቸው እየሸመቱ እንደሚገኙ የጠቀሱት ወይዘሮ ሃይማኖት ያልተገባ ዋጋ በሚጨምሩ ነጋዴዎች ላይ የሚደረገው ቁጥጥር መጠናከር እንዳለበት አመልክተዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026