የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ለትንሳኤ በዓል የግብርና ምርቶች የአቅርቦት እጥረት እንዳይፈጠር የተለያዩ ተግባራት ተከናውነዋል

Apr 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሐረር ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በሐረር ከተማ ለትንሳኤ በዓል የሚያስፈልጉ የግብርና ምርቶች የአቅርቦት እጥረት እንዳይፈጠር የሚያስችሉ ተግባራት መከናወናቸውን የክልሉ ንግድ ልማት ኤጀንሲ ገለጸ።

ለበዓሉ የሚያስፈልጉ የግብርና ምርት አቅርቦት በበቂ ሁኔታ መኖሩንም ሻጭና ሸማቾች ተናግረዋል።

የሐረሪ ክልል ንግድ ልማት ኤጀንሲ ሃላፊ አቶ ሸሪፍ ሙሜ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ለበዓሉ የሚያስፈልጉ ምርቶች እጥረት እንዳይከሰት ከሁሉም የንግዱ ማህበረሰብ ጋር ውይይት ተደርጓል።

የምርት አቅርቦትን ከማሳለጥ አንጻርም ከክልሉ ገጠር ወረዳዎች የሚመረተውን ምርት ወደ ከተማው የማቅረብና ከተለያዩ አቅራቢዎች ጋር ትስስር በመፍጠር ምርት ወደ ከተማው እንዲገባ መደረጉን ተናግረዋል።

እንዲሁም የምስራቅ እዝ ያመረተውን ምርት ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲዳረስ ለሸማቾች ማህበራት እያቀረበ መሆኑንም አመልክተዋል።

በተጨማሪም በከተማው የቅዳሜ እና እሁድ ገበያ ስፍራዎችን የማጠናከር ስራ መስራቱን ጠቁመዋል።

ከዚሁ ጎን ለጎን ያልተገባ ዋጋ የሚጨምሩ ነጋዴዎችን የመከታተልና የመቆጣጠር ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመው በአሁኑ ወቅት ለበዓሉ የሚያስፈልጉ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ግብይት እየተፈጸመ መሆኑን አመልክተዋል።

በከተማው በተለምዶ ሞቢል በተባለው የቅዳሜና እሁድ ገበያ በአትክልት ሽያጭ የተሰማሩት ወይዘሮ በቀለች ንጉሴ ከአካባቢውና ከሌሎች ስፍራ አትክልት ለተጠቃሚው እያቀረቡ መሆኑን ጠቅሰዋል።


ምርቱን በተመጣጣኝ ዋጋ በመሸጥ ህዝቡ በዓሉን በደስታ እንዲያሳልፍ ጥረት እያደረጉ እንደሚገኙ ገልጸዋል።

የበዓል ገበያ የምርት አቅርቦቱ የተሻለ መሆኑንና የክልሉ ንግድ ጽህፈት ቤት ባወጣው ዋጋ መሰረት ለተጠቃሚው በተመጣጣኝ ዋጋ እየሸጡ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የግብርና ምርት ነጋዴ የሆኑት ኢሳያስ አለማየሁ ናቸው።


ለትንሳኤ በዓል አትክልት፣ እንቁላልና ሌሎችም ምርቶች አቅርቦት መኖሩን የተናገሩት ደግሞ በስፍራው አትክልት በመሸመት ላይ የነበሩት ወይዘሮ ሃይማኖት የሺጥላ ናቸው።


ለበዓሉም የሚያስፈልገውን በአቅማቸው እየሸመቱ እንደሚገኙ የጠቀሱት ወይዘሮ ሃይማኖት ያልተገባ ዋጋ በሚጨምሩ ነጋዴዎች ላይ የሚደረገው ቁጥጥር መጠናከር እንዳለበት አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025