🔇Unmute
አሶሳ፤ ሚያዚያ 2/2018 (ኢዜአ)- በአሶሳ ከተማ ለትንሳኤ በዓል ገበያ የሚሆን በቂ የግብርናና የፍጆታ ምርቶች አቅርቦት መኖሩን ሸማቾች እና አቅራቢዎች ተናገሩ።
በአሶሳ ከተማ የገበያ ማዕከል ኢዜአ ያነጋገርናቸው ሸማቾች እና አቅራቢዎች እንደተናገሩት የወቅቱ የትራንስፖርት ችግር ፈተና ቢሆንም ለበዓሉ የግብርናና የፍጆታ ምርቶች በበቂ ሁኔታ ይገኛሉ።
ለበዓል የሚሆኗቸውን ምርቶች ሲሸምቱ ያገኘናቸው ወይዘሮ ህይወት ሀይሉ እና ወጣት አበበ አዳነ እንደተናገሩት፤ በገበያው በቂ የግብርና ምርቶች ቢኖሩም መጠነኛ የዋጋ ጭማሪ ታይቷል።

ይህም የወቅቱን የትራንስፖርት እጥረት ያገናዘበ በመሆኑ ሁሉም እንደሚረዳው የገለጹት ነዋሪዎቹ፣ በገበያው የተጋነነ የዋጋ ጭማሪ እንዳይኖር በመንግስት የተሰራው ስራ በተመጣጣኝ ዋጋ ለመሸመት እንዳስቻላቸው ተናግረዋል።
በከተማዋ ለበዓሉ የግብርናና የፍጆታ ምርቶች በበቂ ሁኔታ መቅረቡን ጠቁመዋል።

በግብርና ምርቶች አቅርቦት ሥራ ላይ የተሰማሩት ሱራፌል በላይ እና መዝገብ አይኑ በበኩላቸው፤ እስካሁን ለበዓል ተብሎ የተለየ የዋጋ ጭማሪ እንዳልተደረገ ተናግረዋል።
በቂ የምርት አቅርቦት በመኖሩ ሸማቾች በፈለጉት አማራጭ እየተገበያዩ እንደሆነ ጠቅሰው፣ ምርትን የሚደብቁ እና ያለአግባብ የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ ነጋዴዎች ላይ አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ ይገባል ብለዋል።
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ አስር ኢብራሂም የትንሣኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ የዋጋ ንረት እና የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት ከአምራቾች እና ከማህበራት ጋር በመቀናጀት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
ቢሮው ያለአግባብ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ አካላት ላይ እየወሰደ ያለውን እርምጃ አጠናክሮ በመቀጠል የተረጋጋ የገበያ ለመፍጠር ከታችኛው መዋቅር ጋር እየሰራ መሆኑንም ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅትም በክልሉ ለበዓሉ የሚሆኑ በቂ የግብርናና የፍጆታ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ እየቀረቡ መሆናቸውን አክለዋል።
በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...
Sep 14, 2026
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026