የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በአሶሳ ከተማ ለበዓል ገበያ የግብርናና የፍጆታ ምርቶች በበቂ ሁኔታ ቀርበዋል

Apr 12, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ ሚያዚያ 2/2018 (ኢዜአ)- በአሶሳ ከተማ ለትንሳኤ በዓል ገበያ የሚሆን በቂ የግብርናና የፍጆታ ምርቶች አቅርቦት መኖሩን ሸማቾች እና አቅራቢዎች ተናገሩ።

በአሶሳ ከተማ የገበያ ማዕከል ኢዜአ ያነጋገርናቸው ሸማቾች እና አቅራቢዎች እንደተናገሩት የወቅቱ የትራንስፖርት ችግር ፈተና ቢሆንም ለበዓሉ የግብርናና የፍጆታ ምርቶች በበቂ ሁኔታ ይገኛሉ።

ለበዓል የሚሆኗቸውን ምርቶች ሲሸምቱ ያገኘናቸው ወይዘሮ ህይወት ሀይሉ እና ወጣት አበበ አዳነ እንደተናገሩት፤ በገበያው በቂ የግብርና ምርቶች ቢኖሩም መጠነኛ የዋጋ ጭማሪ ታይቷል።


ይህም የወቅቱን የትራንስፖርት እጥረት ያገናዘበ በመሆኑ ሁሉም እንደሚረዳው የገለጹት ነዋሪዎቹ፣ በገበያው የተጋነነ የዋጋ ጭማሪ እንዳይኖር በመንግስት የተሰራው ስራ በተመጣጣኝ ዋጋ ለመሸመት እንዳስቻላቸው ተናግረዋል።

በከተማዋ ለበዓሉ የግብርናና የፍጆታ ምርቶች በበቂ ሁኔታ መቅረቡን ጠቁመዋል።


በግብርና ምርቶች አቅርቦት ሥራ ላይ የተሰማሩት ሱራፌል በላይ እና መዝገብ አይኑ በበኩላቸው፤ እስካሁን ለበዓል ተብሎ የተለየ የዋጋ ጭማሪ እንዳልተደረገ ተናግረዋል።

በቂ የምርት አቅርቦት በመኖሩ ሸማቾች በፈለጉት አማራጭ እየተገበያዩ እንደሆነ ጠቅሰው፣ ምርትን የሚደብቁ እና ያለአግባብ የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ ነጋዴዎች ላይ አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ ይገባል ብለዋል።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ አስር ኢብራሂም የትንሣኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ የዋጋ ንረት እና የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት ከአምራቾች እና ከማህበራት ጋር በመቀናጀት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ቢሮው ያለአግባብ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ አካላት ላይ እየወሰደ ያለውን እርምጃ አጠናክሮ በመቀጠል የተረጋጋ የገበያ ለመፍጠር ከታችኛው መዋቅር ጋር እየሰራ መሆኑንም ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅትም በክልሉ ለበዓሉ የሚሆኑ በቂ የግብርናና የፍጆታ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ እየቀረቡ መሆናቸውን አክለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026