የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በድሬዳዋ በሸቀጦች ላይ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ እንዳይደረግ ቁጥጥር እየተደረገ ነው 

Apr 12, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ድሬደዋ ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በአልን ምክንያት በማድረግ በሸቀጦች ላይ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ እንዳይደረግ ቁጥጥርና ክትትል እየተደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ገለፀ።

ሸማቾች በበኩላቸው ለትንሳኤ በዓል የግብርናና የኢንዱስትሪ ውጤቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እየገዙ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ንግድ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሚኖ ጣሃ ለኢዜአ እንደገለፁት ፤ የነዳጅ እጥረትና በአልን ምክንያት በማድረግ በግብርናና በኢንዱስትሪ ምርቶች ላይ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ አካላትን በህግ ተጠያቂ ለማድረግ ግብረ ኃይል ተቋቁሞ ወደ ስራ ተገብቷል።

ግብረ ሀይሉ ከህብረተሰቡ በሚደርሰው ጥቆማና መረጃዎች መሰረት የኢንዱስትሪ ምርቶች ላይ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ በማያደርጉና እጥረት ለመፍጠር የሚፈልጉ አካላትን በህግ ተጠያቂ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት የሚፈልጉ ጥቂት ነጋዴዎች ወቅታዊ ሁኔታን በመጠቀም በህዝቡ ላይ የሚያደርሱትን ጫና ለመከላከል ጠንካራ ክትትል እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።

ከዚህ ጎን ለጎን ግብረ ኃይሉ የልኳንዳ ቤቶች የትንሳኤ በአልን ምክንያት በማድረግ በስጋ ዋጋ ላይ ጭማሬ እንዳያደርጉ መግባባት ላይ መደረሱን አቶ አሚኖ ገልጸዋል ።

በማህበራትና ዩኒየኖች እንዲሁም በባዛሮችና በቅዳሜና እሁድ ገበያዎች በኩል ለትንሳኤ በአል የፍጆታ ምርቶች በበቂ ሁኔታ መቅረባቸውንም አስታውቀዋል ።

በቅዳሜና እሁድ ገበያ እና ለበዓል በተዘጋጀው የንግድ ባዛር ላይ ምርቶችን ሲሸምቱ የነበሩት ወይዘሮ ትርሲት ጌታቸው እና ወይዘሮ ትቅደም አሰፋ ለበዓል በቂ የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶች መቅረባቸውን ተናግረዋል።

ምርቶቹን በተመጣጣኝ ዋጋ መግዛታቸውን ጠቅሰው አስተዳደሩ እያደረገ የሚገኘውን ቁጥጥርና ክትትል ማጠናከር እንዳለበት ገልጸዋል ።

በምርቶች ላይ ያልተገባ የዋጋ ጭማሬ የሚያደርጉ ነጋዴዎች ተጠያቂ እንዲሆኑ የድርሻቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026