የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ለትንሳኤ በዓል የሚሆኑ የፍጆታ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እና በበቂ ሁኔታ እያገኘን ነው

Apr 12, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 3/2018 (ኢዜአ)፦ ለትንሳኤ በዓል የሚሆኑ የፍጆታ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እና በበቂ ሁኔታ እያገኙ መሆኑን ኢዜአ ያነጋገራቸው ሸማቾች ተናገሩ፡፡

በመዲናዋ የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ የተዘጋጁ የንግድ ባዛሮች የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶች ለሸማቾች ሰፊ አማራጭ ይዘው ቀርበዋል።

በተለይም እንደ እንቁላል፣ ቅቤ፣ ሽንኩርትና የቅመማ ቅመም ዓይነቶች እንዲሁም የባህል አልባሳት በከፍተኛ መጠን እየቀረቡ ይገኛል።

የምርት አቅርቦቱን አስመልክቶ ኢዜአ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች እንደገለጹት፤ አስፈላጊ የበዓል ግብዓት በበቂ ሁኔታ ማግኘት ችለዋል። ከበዓሉ ጋር ተያይዞ ካለው ፍላጎት አኳያም የዋጋው ሁኔታ ተመጣጣኝ ነው።

ከሸማቾች መካከል አስተያየታቸውን የሰጡት አቶ እሸቱ ተሾመ እንዳሉት፤ በመዲናዋ በተዘጋጁ የተለያዩ ባዛሮች ላይ ለበዓል የሚያስፈልጉ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ አግኝተዋል።

ሌላኛው ሸማች አቶ ጸጋዬ ደምሴ በበኩላቸው፤ በተዘጋጀው ኤግዚብሽንና ባዛር የሚፈልጓቸውን ዕቃዎች በአንድ ቦታና በተመጣጣኝ ዋጋ መግዛት መቻላቸውን ተናግረዋል።

ለበዓሉ አስፈላጊ የሆኑ ምርቶችን ከአምራቾች በቀጥታ ማግኘት ችያለሁ ያሉት ደግሞ አቶ አብርሃም ቦጋለ ናቸው።

በባዛሩ ላይ የባህል አልባሳትን ያቀረቡት ነጋዴ ትርሲት አበበ በበኩላቸው በመደበኛ ሱቆች ከሚሸጡበት ዋጋ በቅናሽ ማቅረባቸውን በመግለጽ፤ ህብረተሰቡም የቀረበውን የዋጋ አማራጭ በመጠቀም እየገዛ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በተመሳሳይ መልኩ የማር ምርት ይዘው የቀረቡት አቶ አብርሃም ሞላ፤ በተመጣጣኝ ዋጋ ለገበያ ማቅረባቸውንና ሸማቹም በአቅርቦቱ ረክቶ ግብይት እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

የቆዳ ውጤቶችን ለገበያ ያቀረበችው ነጋዴ ፋይዛ ኸይሩ እንደተናገረችው፤ ሸማቹ ለበዓል ስጦታ የሚሆኑ ዕቃዎችን እየገዛ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026