የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

Apr 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት መሆኑ ተገለጸ።

‎የአፋር ክልል ገቢዎች ቢሮ፤ የከተማ አስተዳደሮችና ዞኖች የስራ ሀላፊዎች ቡድን ከአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ልምድ ወስደዋል።

የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮም በቴክኖሎጂ በታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስራው ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ 66 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ መቻሉን አስታውቋል።


‎የአፋር ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ አቶ አወል አብዲ በጉብኝቱ ላይ እንደገለጹት፤ የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ በአሰራር፣ በአደረጃጀትና በቴክኖሎጂ የተደራጀው አሰራሩ ጥሩ ልምድ የሚወሰድበት ነው።

የልምድ ልውውጡም በአፋር ክልል ገቢ አሰባሰብ ስራው ላይ ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ተናግረዋል።

ዘመናዊ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂን በመተግበር ፈጣን፣ ግልጽና ተጠያቂነት ያለው አሰራር ለማስፈን የተደረገው ጥረት ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ ለመሰብሰብ መሰረት መሆኑንም ለመገንዘብ መቻላቸውንም ገልጸዋል።

የክልሉን ህዝብ የልማትና የሰላም ፍላጎት ለማሟላት የሚቻለው ያለውን ሃብት በአግባቡ በመለየት በተገቢው መሰብሰብ ሲቻል መሆኑንም ገልፀዋል።

የሰመራ ሎጊያ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አብዱሙሳ ሁሴን በበኩላቸው፤ የአማራ ክልል በገቢ አሰባሰብ ዘርፍ እያከናወነ ያለው ሁሉን አቀፍ ተግባራትን ለመገንዘብ መቻላቸውን ገልፀዋል።


አሁን ላይ በአሰራር፣ በቴክኖሎጂ አጠቃቀምና ትግበራ እንዲሁም በህግ ማእቀፍ ዝግጅት ያገኙትን ልምድ ወደ ከተማ አስተዳደራቸው ወስደው በመተግበር ገቢን አሟጦ በመሰብሰብ ለልማት ለማዋል ቁርጠኝነትን እንደፈጠረባቸው ተናግረዋል።

የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ሃላፊ መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 66 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ ተችሏል።

በተለይም የ'ኤሌክትሮኒክስ ታክስ አድሚኒስትሬሽን ሲስተም' ተግባራዊ በመደረጉ ትልቅ ውጤት ለማስመዝገብ እንደተቻለም ጠቅሰዋል።


በተጨማሪም ለባለሙያዎች ግንዛቤ በመፍጠር በተሟላ መንገድ እስከታች ድረስ እንዲተገበር መደረጉን አስገንዝበዋል።

‎ይህም ማሕበረሰቡ መብትና ግዴታውን በመገንዘብ የሚጠበቅበትን ግብር በፍትሃዊነት፣ በግልጽነትና ከብልሹ አሰራር በጸዳ መልኩ እንዲከፍል እድል የፈጠረ መሆኑን አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026