የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ኢትዮጵያ ፈተናዎችን ወደ እድል በመቀየር በኢንዱስትሪው ዘርፍ ተጨባጭ ለውጥ እያስመዘገበች ነው- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

Apr 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ያጋጠሟትን ፈተናዎች ወደ ዕድል በመቀየር በኢንዱስትሪው ዘርፍ ተጨባጭ ለውጥ እያስመዘገበች መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።

“የሉዓላዊነት ልብ” በሚል ርዕሰ ጉዳይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር ቆይታ አድርገዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው የኮሮና ወረርሽኝ ያስከተለው ዓለም አቀፍ ቀውስ እና የአጎዋ ስምምነት መቋረጥ ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ነፃነት አዲስ የማንቂያ ደወል መሆናቸውን ገልጸዋል።

እነዚህን ተግዳሮቶች እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም የኢንዱስትሪውን ዘርፍ ለማነቃቃት አራት ስልታዊ ምሰሶዎች ያሉት የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተግባራዊ መደረጉን አስረድተዋል።

ከነዚህ ስልቶች መካከልም ዋነኛው የኢንዱስትሪ መሪነቱን ከመንግሥት ወደ ግሉ ዘርፍ የማሸጋገር ሥራ ሲሆን፣ ይህም በዘርፉ ላይ ከፍተኛ መነቃቃትን መፍጠሩን አመልክተዋል።

በዚህ የለውጥ እርምጃ ማግስት 8 ሺህ ገደማ የነበሩት አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች፣ በአሁኑ ወቅት ከ26 ሺህ በላይ መድረሳቸውን ገልጸዋል።

የንግዱ ማህበረሰብ ፊቱን ወደ አምራችነት እንዲያዞር ካደረገው ተነሳሽነት ጋር ተያይዞ፣ በአሁኑ ወቅት 2 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዜጎች በንግድና ኢንዱስትሪ ዘርፍ የፈቃድ ባለቤት እንዲሆኑ ማስቻሉን በማሳያነት ጠቅሰዋል።

ይህ ዕድገት የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት በ22 ነጥብ 7 በመቶ እንዲጨምር ከማድረጉም ባለፈ፣ ለዘርፉ የሚቀርበው የኃይል መጠን እንዲያድግ ምክንያት መሆኑን ነው ያብራሩት።

ሌላኛው ትኩረት ያረፈው የኢንዱስትሪ ግብዓቶችን በሀገር ውስጥ ምርት መተካት ላይ ሲሆን፣ ቀደም ሲል 90 በመቶ የነበረውን የውጭ ጥገኝነት በከፍተኛ ሁኔታ መቀነስ መቻሉን አስረድተዋል።

በአሁኑ ወቅት እንደ ቢራ ገብስ፣ ጨርቃጨርቅና ስንዴ ያሉ ግብዓቶችን በሀገር ውስጥ ሙሉ በሙሉና በከፊል ማምረት መጀመሩን ጠቁመዋል።

ለዚህ ስኬት በአራት የአግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ዙሪያ የተደራጁ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን አርሶ አደሮች ለፋብሪካዎች ግብዓት በማቅረብ ረገድ የጀርባ አጥንት መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዝርዝር አብራርተዋል።

በተጨማሪም በሀገር ውስጥ የነበሩ ነገር ግን በተለያዩ ማነቆዎች ሥራ አቁመው የነበሩ 800 ገደማ ፋብሪካዎች፣ አስፈላጊው ድጋፍ ተደርጎላቸው ወደ ማምረት መመለሳቸውን ጠቁመዋል።

ይህም የኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም ከነበረበት 47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ከፍ እንዲል በማድረግ፣ በሀገር ውስጥ ምርት ላይ ትልቅ እመርታ መፍጠሩን ገልጸዋል።

የመጨረሻው ስልታዊ ምሰሶ የሆነው ተኪ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ማምረት፣ ቀደም ሲል ለውጭ ምርት ይወጣ የነበረውን 3 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን ማስቻሉን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቆይታቸው አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025