🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 8/2018 (ኢዜአ)፦ የአግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ውጤታማነት እያደገና የኢንቨስትመንት ፍሰት እየጨመረ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ ታረቀኝ ቡልልታ ገለጹ።
የተቀናጁ የአግሮ-ኢንዱስትሪ ፓርኮች የግብርና ምርቶች የሚሰበሰቡባቸው፣ የሚቀነባበሩባቸው፣ የታሸጉ ምርቶች ለገበያ የሚቀርቡባቸውና ወደ ውጭ ለመላክ የሚዘጋጁባቸው ማዕከላት ናቸው።
ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን መተካት፣ ምርቶችን እሴት ጨምሮ ወደ ውጭ መላክ፣ የግብርና ምርትን ማዘመንና የሥራ ዕድል መፍጠር ከተቋቋሙባቸው ዓላማዎች መካከል ይጠቀሳሉ።
የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ ታረቀኝ ቡልልታ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ በአሁኑ ወቅት ወደ ስራ የገቡት የይርጋለም፣ ቡልቡላ፣ ቡሬ የአግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ውጤታማነት እያደገ እና የኢንቨስትመንት ፍሰት እየጨመረ ይገኛል።
ሌሎች የአግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮች በስፋት ወደ ስራ ለማስገባት እየተሰራ ነው ብለዋል።
እንደ ሚኒስትር ዴኤታው ገለጻ፤ የግብርና ምርቶች ላይ እሴት በመጨመር ለአገር ውስጥና ለውጭ ገበያ ማዋል ለኢንዱስትሪ እድገት ዋና መሰረት ነው።
አገራት ቀጣይነት ላለው ኢኮኖሚያዊ እድገትና ተወዳዳሪነት እሴት ጨምሮ የሁለተኛና የሶስተኛ ደረጃ ምርቶች መላክ ወሳኝ ነው ብለዋል።
የግብርና ምርቶች ላይ እሴት በመጨመር ለአገር ውስጥና ለውጭ በማቅረብ የአግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።
በሌላ በኩል በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በተከናወኑ ውጤታማ ስራዎች ስራ አቁመው የተዘጉ ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ በማስገባትና አዳዲስ ኢንቨስትመንቶች ወደ ስራ እንዲገቡ ማሰቻሉን አንስተዋል።
በየዓመቱ የሚዘጋጀው ሀገር አቀፍ ኤክስፖና ባዛርም ኢንዱስትሪው የደረሰበትን ደረጃ ከማሳየትና የገበያ ትስስር ከመፍጠር አኳያ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው ብለዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025