🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 8/2018 (ኢዜአ)፦ የአግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ውጤታማነት እያደገና የኢንቨስትመንት ፍሰት እየጨመረ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ ታረቀኝ ቡልልታ ገለጹ።
የተቀናጁ የአግሮ-ኢንዱስትሪ ፓርኮች የግብርና ምርቶች የሚሰበሰቡባቸው፣ የሚቀነባበሩባቸው፣ የታሸጉ ምርቶች ለገበያ የሚቀርቡባቸውና ወደ ውጭ ለመላክ የሚዘጋጁባቸው ማዕከላት ናቸው።
ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን መተካት፣ ምርቶችን እሴት ጨምሮ ወደ ውጭ መላክ፣ የግብርና ምርትን ማዘመንና የሥራ ዕድል መፍጠር ከተቋቋሙባቸው ዓላማዎች መካከል ይጠቀሳሉ።
የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ ታረቀኝ ቡልልታ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ በአሁኑ ወቅት ወደ ስራ የገቡት የይርጋለም፣ ቡልቡላ፣ ቡሬ የአግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ውጤታማነት እያደገ እና የኢንቨስትመንት ፍሰት እየጨመረ ይገኛል።
ሌሎች የአግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮች በስፋት ወደ ስራ ለማስገባት እየተሰራ ነው ብለዋል።
እንደ ሚኒስትር ዴኤታው ገለጻ፤ የግብርና ምርቶች ላይ እሴት በመጨመር ለአገር ውስጥና ለውጭ ገበያ ማዋል ለኢንዱስትሪ እድገት ዋና መሰረት ነው።
አገራት ቀጣይነት ላለው ኢኮኖሚያዊ እድገትና ተወዳዳሪነት እሴት ጨምሮ የሁለተኛና የሶስተኛ ደረጃ ምርቶች መላክ ወሳኝ ነው ብለዋል።
የግብርና ምርቶች ላይ እሴት በመጨመር ለአገር ውስጥና ለውጭ በማቅረብ የአግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።
በሌላ በኩል በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በተከናወኑ ውጤታማ ስራዎች ስራ አቁመው የተዘጉ ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ በማስገባትና አዳዲስ ኢንቨስትመንቶች ወደ ስራ እንዲገቡ ማሰቻሉን አንስተዋል።
በየዓመቱ የሚዘጋጀው ሀገር አቀፍ ኤክስፖና ባዛርም ኢንዱስትሪው የደረሰበትን ደረጃ ከማሳየትና የገበያ ትስስር ከመፍጠር አኳያ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው ብለዋል።
በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...
Sep 14, 2026
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026