🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦በሸገር ከተማ ካለው የመልማት አቅም ጋር የሚመጣጠን ኢንቨስትመንትን መሳብ የሚያስችል ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አቶ ጉዮ ገልገሎ ገለጹ።
በከተማዋ የኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ልማት ጽሕፈት ቤት አዘጋጅነት የሚዲያ አካላትን ያሳተፈ የኢንቨስትመንት ሥራዎች የመስክ ምልከታ ተካሄዷል።
በዚሁ መርሐ ግብር በገላንና በየካ ጣፎ ክፍለ ከተሞች የሚገኙ የተለያዩ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችና የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪዎች ተጎብኝተዋል።
የከተማዋ ምክትል ከንቲባ አቶ ጉዮ በጉብኝቱ ወቅት እንደገለጹት፤ ከተማዋ ያላትን የኢንቨስትመንት ዕድሎችና አቅም ተጠቅማ የኢኮኖሚ ማዕከል እንድትሆን እየተሰራ ይገኛል።
ይህም የከተማዋን የኢኮኖሚ ዕድገት ከመደገፍ ባለፈ የብልጽግና ጉዞን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ውስጥ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ገልጸዋል።

ከተማዋ ከአዲስ አበባ ጋር ያላት ቅርበት ለሎጂስቲክስ ማዕከልነት ምቹ እንደሚያደርጋት ጠቅሰው፥ ያለው ሰፊ የተፈጥሮ ሀብት ለንግድና ለኢንቨስትመንት መስፋፋት ትልቅ ዕድል መሆኑን ተናግረዋል።
አሁን ላይ በከተማዋ እየተከናወኑ ያሉ የኢንቨስትመንት ሥራዎችም ካለው አቅም ጋር የሚመጣጠን እንዲሆን ምቹ ሁኔታዎች እየተፈጠሩ መሆኑን ገልጸዋል።
ከተማዋ ከተመሰረተችበት ጊዜ ጀምሮ እስካሁን በተከናወኑ ተግባራት በኢንቨስትመንት ዘርፉ ውጤታማነት እየታየና በርካታ ስኬቶች እየተመዘገቡ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በከተማ አስተዳደሩ በኢንቨስትመንት ላይ ከተሰማሩ ድርጅቶች መካከል የዊንፊልድ ትሬዲንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ናደው ጥላሁን፤ የሸገር ከተማ አስተዳደር ባመቻቸው የኢንቨስትመንት ዕድል በተሽከርካሪ ንግድ ዘርፍ መሰማራታቸውን ገልጸዋል።
በዚህም ከ200 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውንና ወደፊትም ፕሮጀክቱን ለማስፋት ትኩረት ሰጥተው እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።
የብራይተን ትሬዲንግ ባለቤትና ሥራ አስኪያጅ አቶ ያዳታ ጁነዲን በበኩላቸው፤ ትልቅ የማምረቻ ፋብሪካ አቋቁመው እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።
እነዚህ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች በዘመናዊ ተሽከርካሪዎች ጥገናና ሽያጭ ላይ የሚሰሩ ሲሆን፤ይህም የአቅርቦት እጥረትን ከመቅረፍ ባለፈ የሥራ ዕድል በመፍጠር ለከተማዋና ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት መፋጠን ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው ተገልጿል።
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025