🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦በሸገር ከተማ ካለው የመልማት አቅም ጋር የሚመጣጠን ኢንቨስትመንትን መሳብ የሚያስችል ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አቶ ጉዮ ገልገሎ ገለጹ።
በከተማዋ የኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ልማት ጽሕፈት ቤት አዘጋጅነት የሚዲያ አካላትን ያሳተፈ የኢንቨስትመንት ሥራዎች የመስክ ምልከታ ተካሄዷል።
በዚሁ መርሐ ግብር በገላንና በየካ ጣፎ ክፍለ ከተሞች የሚገኙ የተለያዩ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችና የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪዎች ተጎብኝተዋል።
የከተማዋ ምክትል ከንቲባ አቶ ጉዮ በጉብኝቱ ወቅት እንደገለጹት፤ ከተማዋ ያላትን የኢንቨስትመንት ዕድሎችና አቅም ተጠቅማ የኢኮኖሚ ማዕከል እንድትሆን እየተሰራ ይገኛል።
ይህም የከተማዋን የኢኮኖሚ ዕድገት ከመደገፍ ባለፈ የብልጽግና ጉዞን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ውስጥ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ገልጸዋል።

ከተማዋ ከአዲስ አበባ ጋር ያላት ቅርበት ለሎጂስቲክስ ማዕከልነት ምቹ እንደሚያደርጋት ጠቅሰው፥ ያለው ሰፊ የተፈጥሮ ሀብት ለንግድና ለኢንቨስትመንት መስፋፋት ትልቅ ዕድል መሆኑን ተናግረዋል።
አሁን ላይ በከተማዋ እየተከናወኑ ያሉ የኢንቨስትመንት ሥራዎችም ካለው አቅም ጋር የሚመጣጠን እንዲሆን ምቹ ሁኔታዎች እየተፈጠሩ መሆኑን ገልጸዋል።
ከተማዋ ከተመሰረተችበት ጊዜ ጀምሮ እስካሁን በተከናወኑ ተግባራት በኢንቨስትመንት ዘርፉ ውጤታማነት እየታየና በርካታ ስኬቶች እየተመዘገቡ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በከተማ አስተዳደሩ በኢንቨስትመንት ላይ ከተሰማሩ ድርጅቶች መካከል የዊንፊልድ ትሬዲንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ናደው ጥላሁን፤ የሸገር ከተማ አስተዳደር ባመቻቸው የኢንቨስትመንት ዕድል በተሽከርካሪ ንግድ ዘርፍ መሰማራታቸውን ገልጸዋል።
በዚህም ከ200 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውንና ወደፊትም ፕሮጀክቱን ለማስፋት ትኩረት ሰጥተው እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።
የብራይተን ትሬዲንግ ባለቤትና ሥራ አስኪያጅ አቶ ያዳታ ጁነዲን በበኩላቸው፤ ትልቅ የማምረቻ ፋብሪካ አቋቁመው እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።
እነዚህ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች በዘመናዊ ተሽከርካሪዎች ጥገናና ሽያጭ ላይ የሚሰሩ ሲሆን፤ይህም የአቅርቦት እጥረትን ከመቅረፍ ባለፈ የሥራ ዕድል በመፍጠር ለከተማዋና ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት መፋጠን ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው ተገልጿል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026