የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ሪፎርሙ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ፈተናዎችን የመቋቋም አቅሙ እንዲጠናከር አድርጓል

Apr 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገር በቀል ሪፎርሙ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ፈተናዎችን የመቋቋም አቅሙን ማጠናከሩን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ (ዶ/ር) ገለጹ።

የ2026 የዓለም ባንክ እና የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) የፀደይ ወቅት ስብሰባ በዋሺንግተን ዲሲ እየተካሄደ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዢ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) አይኤምኤፍ “ከአዲሱ ዓለም አቀፍ ፋይናንስ ስነ-ምህዳር ጋር መጣጣም” በሚል ርዕስ ባዘጋጀው ከፍተኛ የፓናል ውይይት ላይ ተሳትፈዋል።

በወቅቱም ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ አቅርቦት በተገደበበት በዚህ ወቅት፣ በሀገር በቀል የሪፎርም እርምጃዎች አማካኝነት ፈታኝ ሁኔታዎችን እንዴት እየተወጣች እንደምትገኝ አብራርተዋል።

እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) በንግግራቸው የኢትዮጵያን አጠቃላይ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ሪፎርም ዋና ዋና ነጥቦች አንስተዋል።

ሪፎርሙ የምንዛሬ ተመን ማዕቀፍን ማጠናከር፣ የገንዘብ ፖሊሲን ማዘመን፣ የሀገር ውስጥ ሀብት አሰባሰብን ማሳደግ እና ኢኮኖሚው ይበልጥ በግል ዘርፍ የሚመራ እንዲሆን ለማድረግ የሚከናወኑ መዋቅራዊ ሪፎርሞችን ያካተተ መሆኑን ገልጸዋል።


የኢኮኖሚው የመቋቋም አቅም መጠናከር በወጪ ንግድ፣ በውጭ ምንዛሬ ክምችትና በገቢ አሰባሰብ ላይ ተጨባጭ ለውጥ እያመጣ መሆኑን የባንኩ ገዥ አመልክተዋል።

ምንም እንኳን የኢትዮጵያ ሪፎርም በሀገር ውስጥ ባለቤትነት የሚመራ ቢሆንም፣ የልማት አጋሮች የሚያደርጉት የተቀናጀ ድጋፍ ለውጤታማነቱ አስፈላጊ መሆኑን ገዢው አስገንዝበዋል።

በተለይም ዓለም አቀፋዊ አለመረጋጋት በግልጽ በሚታይበት በዚህ ወቅት፣ ሀገራዊ የልማት ጥረቶችን ለማሳካት የልማት አጋሮች የሚያደርጉት ድጋፍ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል።

ይህ የፓናል ውይይት ኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋትን ለመጠበቅ፣ ሪፎርሞችን ለማስቀጠል እና ተለዋዋጭ በሆኑ ዓለም አቀፍ ተግዳሮቶች ውስጥ ይበልጥ ጠንካራና ሁሉን አቀፍ ኢኮኖሚ ለመገንባት ያላትን ቁርጠኝነት ዳግም ያረጋገጠ ሆኗል።

ገዢው በሀገር ደረጃ እያደገ የመጣውን የለውጥና የብልጽግና ፍላጎት በማንሳት፣ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ተምሳሌት (Beacon) የመሆን ጉዞ ላይ እንደሆነች ገልጸዋል።

በውይይቱ ላይ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ አይበገሬነት አድናቆት እንዳገኘ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026