🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ስትራቴጂያዊ አጋርነታቸውን እንደሚያጠናክሩ ገለጹ።
በገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ የተመራ ልዑክ በዋሽንግተን ዲሲ እየተካሄደ ካለው የ2026 የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይኤምኤፍ) እና ዓለም ባንክ የጸደይ ወቅት ስብሰባ ጎን ለጎን ከአውሮፓ ኅብረት የዓለም አቀፍ አጋርነት ኮሚሽነር ጆሴፍ ሲኬላ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አካሂዷል።
ውይይቱ በኢትዮጵያ እና በአውሮፓ ህብረት መካከል ያለውን ስትራቴጂክ አጋርነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ ያለመ መሆኑም ተገልጿል።

በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለውን ኢኮኖሚያዊ ትብብር ማሳደግ ላይ ያተኮረ እንደነበርም ኢዜአ ከገንዘብ ሚኒስቴር ያገኘው መረጃ ያመላክታል።
የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ማሻሻያ ለመደገፍ፣ የኢንቨስትመንት ምህዳሩን ይበልጥ ለማሻሻል፣ የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም በሚያስችሉ ስራዎች እና ቀጣይነት ባለው የኢኮኖሚ እድገት ግቦች ላይ በትብብር ለመስራት አቅጣጫ መቀመጡም ተገልጿል።
ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የጋራ ተጠቃሚነታቸውን በሚያረጋግጥ መልኩ ትብብራቸውን ለማጠናከር ቁርጠኝነታቸውን ማረጋገጣቸውም ተመላክቷል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026