🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ስትራቴጂያዊ አጋርነታቸውን እንደሚያጠናክሩ ገለጹ።
በገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ የተመራ ልዑክ በዋሽንግተን ዲሲ እየተካሄደ ካለው የ2026 የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይኤምኤፍ) እና ዓለም ባንክ የጸደይ ወቅት ስብሰባ ጎን ለጎን ከአውሮፓ ኅብረት የዓለም አቀፍ አጋርነት ኮሚሽነር ጆሴፍ ሲኬላ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አካሂዷል።
ውይይቱ በኢትዮጵያ እና በአውሮፓ ህብረት መካከል ያለውን ስትራቴጂክ አጋርነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ ያለመ መሆኑም ተገልጿል።

በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለውን ኢኮኖሚያዊ ትብብር ማሳደግ ላይ ያተኮረ እንደነበርም ኢዜአ ከገንዘብ ሚኒስቴር ያገኘው መረጃ ያመላክታል።
የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ማሻሻያ ለመደገፍ፣ የኢንቨስትመንት ምህዳሩን ይበልጥ ለማሻሻል፣ የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም በሚያስችሉ ስራዎች እና ቀጣይነት ባለው የኢኮኖሚ እድገት ግቦች ላይ በትብብር ለመስራት አቅጣጫ መቀመጡም ተገልጿል።
ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የጋራ ተጠቃሚነታቸውን በሚያረጋግጥ መልኩ ትብብራቸውን ለማጠናከር ቁርጠኝነታቸውን ማረጋገጣቸውም ተመላክቷል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025