የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ኢትዮጵያ እና የጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ጃይካ) የልማት ትብብራቸውን የበለጠ ያጠናክራሉ

Apr 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ እና የጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ጃይካ) የልማት ትብብራቸውን የበለጠ እንደሚያጠናክሩ አስታወቁ፡፡

በገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክ የ2026 የዓለም ገንዘብ ድርጅትና የዓለም ባንክ የጸደይ ወቅት ስብሰባ ጎን ለጎን ከጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ጃይካ) ምክትል ፕሬዚዳንት ናኦኪ አንዶ ጋር ተወያይቷል፡፡

ሚኒስትሩ አህመድ ሺዴ ኢትዮጵያ ከጃፓን ብሎም ከጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ጃይካ) ጋር ላላት የረጅም ጊዜ ትብብር አድናቆታቸውን ገልጸዋል፡፡

በተለይም በመሠረተ ልማት፣ ግብርና፣ ጤና፣ ትምህርት፣ በፋይናንስ፣ ቴክኒክ እና በአቅም ግንባታ ዘርፎች ላይ ኤጀንሲው እያደረገ ላለው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል፡፡


ሚኒስትሩ አህመድ ሺዴ ለምክትል ፕሬዚዳንቱ የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ በተመለከተም ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

ጃይካ በአቪየሽን፤ በኀይል ልማት እና በመንገድ መሰረተ ልማተ ዘርፎች የሚያደርገውን ድጋፍ እንዲያጠናክር መጠየቃቸውን ኢዜአ ከገንዘብ ሚኒስቴር ያገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡

ኢትዮጵያ ለምታዘጋጀው የኮፕ 32 ጉባዔ እያደረገች ባለው ዝግጅት ላይም የተወያዩ ሲሆን ጃይካ በአየር ንብረት መቋቋምና አረንጓዴ ልማት እቅዶች ላይ እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል።

የጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ጃይካ) ምክትል ፕሬዚዳንት ናኦኪ አንዶ በበኩላቸው፤ ጃይካ ለኢትዮጵያ የልማት አጀንዳ የሚሰጠውን ድጋፍ እንደሚቀጥልና በተመሳሳይም ቅድሚያ በሚሰጣቸው መስኮች ላይ ትብብሩን እንደሚያጠናክር አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025