የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ኢትዮጵያ እና የጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ጃይካ) የልማት ትብብራቸውን የበለጠ ያጠናክራሉ

Apr 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ እና የጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ጃይካ) የልማት ትብብራቸውን የበለጠ እንደሚያጠናክሩ አስታወቁ፡፡

በገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክ የ2026 የዓለም ገንዘብ ድርጅትና የዓለም ባንክ የጸደይ ወቅት ስብሰባ ጎን ለጎን ከጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ጃይካ) ምክትል ፕሬዚዳንት ናኦኪ አንዶ ጋር ተወያይቷል፡፡

ሚኒስትሩ አህመድ ሺዴ ኢትዮጵያ ከጃፓን ብሎም ከጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ጃይካ) ጋር ላላት የረጅም ጊዜ ትብብር አድናቆታቸውን ገልጸዋል፡፡

በተለይም በመሠረተ ልማት፣ ግብርና፣ ጤና፣ ትምህርት፣ በፋይናንስ፣ ቴክኒክ እና በአቅም ግንባታ ዘርፎች ላይ ኤጀንሲው እያደረገ ላለው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል፡፡


ሚኒስትሩ አህመድ ሺዴ ለምክትል ፕሬዚዳንቱ የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ በተመለከተም ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

ጃይካ በአቪየሽን፤ በኀይል ልማት እና በመንገድ መሰረተ ልማተ ዘርፎች የሚያደርገውን ድጋፍ እንዲያጠናክር መጠየቃቸውን ኢዜአ ከገንዘብ ሚኒስቴር ያገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡

ኢትዮጵያ ለምታዘጋጀው የኮፕ 32 ጉባዔ እያደረገች ባለው ዝግጅት ላይም የተወያዩ ሲሆን ጃይካ በአየር ንብረት መቋቋምና አረንጓዴ ልማት እቅዶች ላይ እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል።

የጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ጃይካ) ምክትል ፕሬዚዳንት ናኦኪ አንዶ በበኩላቸው፤ ጃይካ ለኢትዮጵያ የልማት አጀንዳ የሚሰጠውን ድጋፍ እንደሚቀጥልና በተመሳሳይም ቅድሚያ በሚሰጣቸው መስኮች ላይ ትብብሩን እንደሚያጠናክር አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026