🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ እና የጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ጃይካ) የልማት ትብብራቸውን የበለጠ እንደሚያጠናክሩ አስታወቁ፡፡
በገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክ የ2026 የዓለም ገንዘብ ድርጅትና የዓለም ባንክ የጸደይ ወቅት ስብሰባ ጎን ለጎን ከጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ጃይካ) ምክትል ፕሬዚዳንት ናኦኪ አንዶ ጋር ተወያይቷል፡፡
ሚኒስትሩ አህመድ ሺዴ ኢትዮጵያ ከጃፓን ብሎም ከጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ጃይካ) ጋር ላላት የረጅም ጊዜ ትብብር አድናቆታቸውን ገልጸዋል፡፡
በተለይም በመሠረተ ልማት፣ ግብርና፣ ጤና፣ ትምህርት፣ በፋይናንስ፣ ቴክኒክ እና በአቅም ግንባታ ዘርፎች ላይ ኤጀንሲው እያደረገ ላለው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

ሚኒስትሩ አህመድ ሺዴ ለምክትል ፕሬዚዳንቱ የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ በተመለከተም ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
ጃይካ በአቪየሽን፤ በኀይል ልማት እና በመንገድ መሰረተ ልማተ ዘርፎች የሚያደርገውን ድጋፍ እንዲያጠናክር መጠየቃቸውን ኢዜአ ከገንዘብ ሚኒስቴር ያገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
ኢትዮጵያ ለምታዘጋጀው የኮፕ 32 ጉባዔ እያደረገች ባለው ዝግጅት ላይም የተወያዩ ሲሆን ጃይካ በአየር ንብረት መቋቋምና አረንጓዴ ልማት እቅዶች ላይ እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል።
የጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ጃይካ) ምክትል ፕሬዚዳንት ናኦኪ አንዶ በበኩላቸው፤ ጃይካ ለኢትዮጵያ የልማት አጀንዳ የሚሰጠውን ድጋፍ እንደሚቀጥልና በተመሳሳይም ቅድሚያ በሚሰጣቸው መስኮች ላይ ትብብሩን እንደሚያጠናክር አረጋግጠዋል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026