የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በኦሮሚያ ክልል ቆላማ አካባቢዎች ድርቅን በዘላቂነት መቋቋም የሚያስችል የመኖ ልማት በልዩ ትኩረት እየተከናወነ ነው

Apr 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ ሚያዝያ 13/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ቆላማ አካባቢዎች ድርቅን በዘላቂነት መቋቋም የሚያስችል የመኖ ልማት በልዩ ትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ መስኖና አርብቶ አደር ልማት ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው በቆላማ እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ድርቅን በዘላቂነት መቋቋም የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑንም ገልጿል።

የቢሮው ምክትል ኃላፊ ሮባ ቱርጬ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ በአርብቶ አደር እና ቆላማ አካባቢዎች በድርቅ ምክንያት በእንስሳት ሀብቱ ላይ የሚደርሰውን ጉዳት የሚቀንሱ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ።

በዚህም በተያዘው በጀት ዓመት ሰፊ መሬት በእንስሳት መኖ የማልማት ስራ እየተከናወነ ሲሆን፣ ይህም ተጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት።


መኖ የሚለማባቸው አካባቢዎች ከእንስሳት ንክኪ ነፃ ሆነው እንዲጠበቁ በማድረግ አርብቶ አደሩ በባለቤትነት እንዲንከባከባቸው እየተደረገ እንደሚገኝም አመላክተዋል።

ሌላው ድርቅን በዘላቂነት ለመቋቋም እየተከናወነ ያለው ተግባር አርብቶ አደሩን ወደ ከፊል አርሶ አደርነት ለመቀየር እየተደረገ ያለው ጥረት አካል መሆኑንም ገልጸዋል።

ለዚህም በክልሉ ቆላማ እና አርብቶ አደር አካባቢዎች አነስተኛ እና መለስተኛ የመስኖ ግድቦችን በመገንባት የቆላ ግብርናን የማልመድ ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በተለይም ባለፉት ስምንት ዓመታት ለሰውና ለእንስሳት መጠጥ ውሃ ቅድሚያ በመስጠት ግንባታቸው ከተጀመሩ 71 አነስተኛና መካከለኛ የመስኖ ግድቦች መካከል 37ቱ በቆላማ አካባቢዎች የሚገኙ ናቸው ብለዋል።


ከእነዚህ 37 ፕሮጀክቶች መካከል 34ቱ ተጠናቅቀው በአሁኑ ወቅት ለሰውና ለእንስሳት መጠጥ፣ ለዓሣ እርባታ እንዲሁም ለመስኖ ልማት አገልግሎት እየሰጡ መሆኑንም አስረድተዋል።

ባለፉት ሁለት ዓመታት በታየው ውጤት ድርቅን በራስ አቅም መቋቋም በመቻሉ፣ ከሌላ አካባቢ ምንም አይነት መኖ አለመጫነኑንም ጨምረው ገልጸዋል።

በክልሉ አርብቶ አደር አካባቢዎች 17 ትላልቅ የመኖ ማከማቻ ማዕከላት እየተገነቡ ሲሆን፣ የመኖ ልማቱን የሚጎዱ መጤ አረሞችን በመከላከል እንዲሁም አካባቢውን በመጠበቅ ልማቱ እንዲጠናከርም መልዕክት አስተላልፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025