የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በኦሮሚያ ክልል ቆላማ አካባቢዎች ድርቅን በዘላቂነት መቋቋም የሚያስችል የመኖ ልማት በልዩ ትኩረት እየተከናወነ ነው

Apr 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ ሚያዝያ 13/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ቆላማ አካባቢዎች ድርቅን በዘላቂነት መቋቋም የሚያስችል የመኖ ልማት በልዩ ትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ መስኖና አርብቶ አደር ልማት ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው በቆላማ እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ድርቅን በዘላቂነት መቋቋም የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑንም ገልጿል።

የቢሮው ምክትል ኃላፊ ሮባ ቱርጬ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ በአርብቶ አደር እና ቆላማ አካባቢዎች በድርቅ ምክንያት በእንስሳት ሀብቱ ላይ የሚደርሰውን ጉዳት የሚቀንሱ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ።

በዚህም በተያዘው በጀት ዓመት ሰፊ መሬት በእንስሳት መኖ የማልማት ስራ እየተከናወነ ሲሆን፣ ይህም ተጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት።


መኖ የሚለማባቸው አካባቢዎች ከእንስሳት ንክኪ ነፃ ሆነው እንዲጠበቁ በማድረግ አርብቶ አደሩ በባለቤትነት እንዲንከባከባቸው እየተደረገ እንደሚገኝም አመላክተዋል።

ሌላው ድርቅን በዘላቂነት ለመቋቋም እየተከናወነ ያለው ተግባር አርብቶ አደሩን ወደ ከፊል አርሶ አደርነት ለመቀየር እየተደረገ ያለው ጥረት አካል መሆኑንም ገልጸዋል።

ለዚህም በክልሉ ቆላማ እና አርብቶ አደር አካባቢዎች አነስተኛ እና መለስተኛ የመስኖ ግድቦችን በመገንባት የቆላ ግብርናን የማልመድ ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በተለይም ባለፉት ስምንት ዓመታት ለሰውና ለእንስሳት መጠጥ ውሃ ቅድሚያ በመስጠት ግንባታቸው ከተጀመሩ 71 አነስተኛና መካከለኛ የመስኖ ግድቦች መካከል 37ቱ በቆላማ አካባቢዎች የሚገኙ ናቸው ብለዋል።


ከእነዚህ 37 ፕሮጀክቶች መካከል 34ቱ ተጠናቅቀው በአሁኑ ወቅት ለሰውና ለእንስሳት መጠጥ፣ ለዓሣ እርባታ እንዲሁም ለመስኖ ልማት አገልግሎት እየሰጡ መሆኑንም አስረድተዋል።

ባለፉት ሁለት ዓመታት በታየው ውጤት ድርቅን በራስ አቅም መቋቋም በመቻሉ፣ ከሌላ አካባቢ ምንም አይነት መኖ አለመጫነኑንም ጨምረው ገልጸዋል።

በክልሉ አርብቶ አደር አካባቢዎች 17 ትላልቅ የመኖ ማከማቻ ማዕከላት እየተገነቡ ሲሆን፣ የመኖ ልማቱን የሚጎዱ መጤ አረሞችን በመከላከል እንዲሁም አካባቢውን በመጠበቅ ልማቱ እንዲጠናከርም መልዕክት አስተላልፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026