🔇Unmute
አዳማ፤ ሚያዝያ 13/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ቆላማ አካባቢዎች ድርቅን በዘላቂነት መቋቋም የሚያስችል የመኖ ልማት በልዩ ትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ መስኖና አርብቶ አደር ልማት ቢሮ አስታወቀ።
ቢሮው በቆላማ እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ድርቅን በዘላቂነት መቋቋም የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑንም ገልጿል።
የቢሮው ምክትል ኃላፊ ሮባ ቱርጬ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ በአርብቶ አደር እና ቆላማ አካባቢዎች በድርቅ ምክንያት በእንስሳት ሀብቱ ላይ የሚደርሰውን ጉዳት የሚቀንሱ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ።
በዚህም በተያዘው በጀት ዓመት ሰፊ መሬት በእንስሳት መኖ የማልማት ስራ እየተከናወነ ሲሆን፣ ይህም ተጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት።

መኖ የሚለማባቸው አካባቢዎች ከእንስሳት ንክኪ ነፃ ሆነው እንዲጠበቁ በማድረግ አርብቶ አደሩ በባለቤትነት እንዲንከባከባቸው እየተደረገ እንደሚገኝም አመላክተዋል።
ሌላው ድርቅን በዘላቂነት ለመቋቋም እየተከናወነ ያለው ተግባር አርብቶ አደሩን ወደ ከፊል አርሶ አደርነት ለመቀየር እየተደረገ ያለው ጥረት አካል መሆኑንም ገልጸዋል።
ለዚህም በክልሉ ቆላማ እና አርብቶ አደር አካባቢዎች አነስተኛ እና መለስተኛ የመስኖ ግድቦችን በመገንባት የቆላ ግብርናን የማልመድ ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በተለይም ባለፉት ስምንት ዓመታት ለሰውና ለእንስሳት መጠጥ ውሃ ቅድሚያ በመስጠት ግንባታቸው ከተጀመሩ 71 አነስተኛና መካከለኛ የመስኖ ግድቦች መካከል 37ቱ በቆላማ አካባቢዎች የሚገኙ ናቸው ብለዋል።

ከእነዚህ 37 ፕሮጀክቶች መካከል 34ቱ ተጠናቅቀው በአሁኑ ወቅት ለሰውና ለእንስሳት መጠጥ፣ ለዓሣ እርባታ እንዲሁም ለመስኖ ልማት አገልግሎት እየሰጡ መሆኑንም አስረድተዋል።
ባለፉት ሁለት ዓመታት በታየው ውጤት ድርቅን በራስ አቅም መቋቋም በመቻሉ፣ ከሌላ አካባቢ ምንም አይነት መኖ አለመጫነኑንም ጨምረው ገልጸዋል።
በክልሉ አርብቶ አደር አካባቢዎች 17 ትላልቅ የመኖ ማከማቻ ማዕከላት እየተገነቡ ሲሆን፣ የመኖ ልማቱን የሚጎዱ መጤ አረሞችን በመከላከል እንዲሁም አካባቢውን በመጠበቅ ልማቱ እንዲጠናከርም መልዕክት አስተላልፈዋል።
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025