🔇Unmute
አዳማ፤ ሚያዝያ 13/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ቆላማ አካባቢዎች ድርቅን በዘላቂነት መቋቋም የሚያስችል የመኖ ልማት በልዩ ትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ መስኖና አርብቶ አደር ልማት ቢሮ አስታወቀ።
ቢሮው በቆላማ እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ድርቅን በዘላቂነት መቋቋም የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑንም ገልጿል።
የቢሮው ምክትል ኃላፊ ሮባ ቱርጬ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ በአርብቶ አደር እና ቆላማ አካባቢዎች በድርቅ ምክንያት በእንስሳት ሀብቱ ላይ የሚደርሰውን ጉዳት የሚቀንሱ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ።
በዚህም በተያዘው በጀት ዓመት ሰፊ መሬት በእንስሳት መኖ የማልማት ስራ እየተከናወነ ሲሆን፣ ይህም ተጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት።

መኖ የሚለማባቸው አካባቢዎች ከእንስሳት ንክኪ ነፃ ሆነው እንዲጠበቁ በማድረግ አርብቶ አደሩ በባለቤትነት እንዲንከባከባቸው እየተደረገ እንደሚገኝም አመላክተዋል።
ሌላው ድርቅን በዘላቂነት ለመቋቋም እየተከናወነ ያለው ተግባር አርብቶ አደሩን ወደ ከፊል አርሶ አደርነት ለመቀየር እየተደረገ ያለው ጥረት አካል መሆኑንም ገልጸዋል።
ለዚህም በክልሉ ቆላማ እና አርብቶ አደር አካባቢዎች አነስተኛ እና መለስተኛ የመስኖ ግድቦችን በመገንባት የቆላ ግብርናን የማልመድ ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በተለይም ባለፉት ስምንት ዓመታት ለሰውና ለእንስሳት መጠጥ ውሃ ቅድሚያ በመስጠት ግንባታቸው ከተጀመሩ 71 አነስተኛና መካከለኛ የመስኖ ግድቦች መካከል 37ቱ በቆላማ አካባቢዎች የሚገኙ ናቸው ብለዋል።

ከእነዚህ 37 ፕሮጀክቶች መካከል 34ቱ ተጠናቅቀው በአሁኑ ወቅት ለሰውና ለእንስሳት መጠጥ፣ ለዓሣ እርባታ እንዲሁም ለመስኖ ልማት አገልግሎት እየሰጡ መሆኑንም አስረድተዋል።
ባለፉት ሁለት ዓመታት በታየው ውጤት ድርቅን በራስ አቅም መቋቋም በመቻሉ፣ ከሌላ አካባቢ ምንም አይነት መኖ አለመጫነኑንም ጨምረው ገልጸዋል።
በክልሉ አርብቶ አደር አካባቢዎች 17 ትላልቅ የመኖ ማከማቻ ማዕከላት እየተገነቡ ሲሆን፣ የመኖ ልማቱን የሚጎዱ መጤ አረሞችን በመከላከል እንዲሁም አካባቢውን በመጠበቅ ልማቱ እንዲጠናከርም መልዕክት አስተላልፈዋል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026