🔇Unmute
አዳማ ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የህብረት ስራ ማህበራትን ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ስትራቴጂ ጋር በማጣጣም የበለጠ ውጤታማ ማድረግ መቻሉን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን ላሌ ገለጹ።
የኢትዮጵያ ህብረት ስራ ኮሚሽን "ወደ ቀበሌ መድረስ" በሚል መሪ ሃሳብ ያዘጋጀው 2ኛው ሀገር አቀፍ የህብረት ስራ ሪፎርም ንቅናቄ መድረክ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ መካሄድ ጀምሯል።

መድረኩን በንግግር የከፈቱት በምክር ቤቱ የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን ላሌ እንደገለጹት፤ በሀገራችን ከሪፎርሙ በፊት በርካታ ህብረት ስራ ማህበራት ቢኖሩም፣ አብዛኞቹ ራሳቸውን ከወቅታዊ ሁኔታ ጋር ያስማሙ አልነበሩም።
በዚህም ምክንያት ዘርፉ ለአባላቱም ሆነ በአጠቃላይ ለሀገር እድገት ሊወጣ የሚገባውን ዘርፈ-ብዙ ጥቅም ሳያስገኝ መቆየቱን አስታውሰዋል።
በአሁኑ ወቅት የማህበራቱን ሚና ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ስትራቴጂ ጋር ለማጣጣም መንግስት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ በመሆኑ ውጤትም እየተገኘ መጥቷል ብለዋል።
መንግስት ለሪፎርሙ ስኬታማነት የ"ስትሪንግ ኮሚቴ" በማደራጀት ድጋፍ እያደረገ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ሰለሞን፤ በአሁኑ ወቅት የማሻሻያ ህግጋት ተዘጋጅተው በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኙና ለዘርፉ የሚሆን ፍኖተ ካርታ መዘጋጀቱንም አስታውቀዋል።
የህብረት ስራ ኮሚሽን "ቀበሌ መድረስ" በሚል መርህ አደራጆችን ያሳተፈ ንቅናቄ መጀመሩ ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣት ፋይዳው የጎላ መሆኑንም ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ህብረት ስራ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጌትነት ታደሰ በበኩላቸው፤ ህብረት ስራ ማህበራት የሀገር ኢኮኖሚ ማሳለጫ እንዲሆኑ አቅጣጫ ተቀምጦ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም ባለፉት ሶስት ዓመታት በጥናት ላይ ተመስርቶ በተደረገ ሪፎርም 31 ሺህ በላይ ማህበራት በስም ብቻ የሚታወቁና አድራሻ የሌላቸው መሆናቸው መለየቱን ተናግረዋል።
በተጨማሪም 5 ሺህ የሚሆኑት ደግሞ ራሳቸውን ችለው መቆም ስለማይችሉ ከሌሎች ጋር እንዲዋሀዱ መደረጉን ጠቅሰዋል።
ከሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ 4 ሺህ የቀበሌ አደራጅ ባለሙያዎች በስልጠናው እየተሳተፉ መሆኑን ጠቅሰው፤ ስልጠናው በተለያዩ ማዕከላት ለተከታታይ ስምንት ቀናት ይሰጣል ብለዋል።
በመድረኮቹም የሀገሪቱን ተጨባጭ ሁኔታና የብልፅግና ጉዞ መሰረት ያደረጉ የዘርፉ ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎች ላይ ሰፊ ውይይት እንደሚደረግ ተመላክቷል።
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025