🔇Unmute
አዳማ ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የህብረት ስራ ማህበራትን ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ስትራቴጂ ጋር በማጣጣም የበለጠ ውጤታማ ማድረግ መቻሉን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን ላሌ ገለጹ።
የኢትዮጵያ ህብረት ስራ ኮሚሽን "ወደ ቀበሌ መድረስ" በሚል መሪ ሃሳብ ያዘጋጀው 2ኛው ሀገር አቀፍ የህብረት ስራ ሪፎርም ንቅናቄ መድረክ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ መካሄድ ጀምሯል።

መድረኩን በንግግር የከፈቱት በምክር ቤቱ የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን ላሌ እንደገለጹት፤ በሀገራችን ከሪፎርሙ በፊት በርካታ ህብረት ስራ ማህበራት ቢኖሩም፣ አብዛኞቹ ራሳቸውን ከወቅታዊ ሁኔታ ጋር ያስማሙ አልነበሩም።
በዚህም ምክንያት ዘርፉ ለአባላቱም ሆነ በአጠቃላይ ለሀገር እድገት ሊወጣ የሚገባውን ዘርፈ-ብዙ ጥቅም ሳያስገኝ መቆየቱን አስታውሰዋል።
በአሁኑ ወቅት የማህበራቱን ሚና ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ስትራቴጂ ጋር ለማጣጣም መንግስት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ በመሆኑ ውጤትም እየተገኘ መጥቷል ብለዋል።
መንግስት ለሪፎርሙ ስኬታማነት የ"ስትሪንግ ኮሚቴ" በማደራጀት ድጋፍ እያደረገ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ሰለሞን፤ በአሁኑ ወቅት የማሻሻያ ህግጋት ተዘጋጅተው በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኙና ለዘርፉ የሚሆን ፍኖተ ካርታ መዘጋጀቱንም አስታውቀዋል።
የህብረት ስራ ኮሚሽን "ቀበሌ መድረስ" በሚል መርህ አደራጆችን ያሳተፈ ንቅናቄ መጀመሩ ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣት ፋይዳው የጎላ መሆኑንም ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ህብረት ስራ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጌትነት ታደሰ በበኩላቸው፤ ህብረት ስራ ማህበራት የሀገር ኢኮኖሚ ማሳለጫ እንዲሆኑ አቅጣጫ ተቀምጦ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም ባለፉት ሶስት ዓመታት በጥናት ላይ ተመስርቶ በተደረገ ሪፎርም 31 ሺህ በላይ ማህበራት በስም ብቻ የሚታወቁና አድራሻ የሌላቸው መሆናቸው መለየቱን ተናግረዋል።
በተጨማሪም 5 ሺህ የሚሆኑት ደግሞ ራሳቸውን ችለው መቆም ስለማይችሉ ከሌሎች ጋር እንዲዋሀዱ መደረጉን ጠቅሰዋል።
ከሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ 4 ሺህ የቀበሌ አደራጅ ባለሙያዎች በስልጠናው እየተሳተፉ መሆኑን ጠቅሰው፤ ስልጠናው በተለያዩ ማዕከላት ለተከታታይ ስምንት ቀናት ይሰጣል ብለዋል።
በመድረኮቹም የሀገሪቱን ተጨባጭ ሁኔታና የብልፅግና ጉዞ መሰረት ያደረጉ የዘርፉ ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎች ላይ ሰፊ ውይይት እንደሚደረግ ተመላክቷል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026