የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

አዲስ ገቢር ነበብ የፖለቲካ ኢኮኖሚ

Apr 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

‎ኢትዮጵያ ቀደም ሲል ከነበረው ግትር ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ አስተሳሰብ ተላቃ፣ ትኩረቱን በተግባራዊ አፈጻጸም ላይ ያደረገ አዲስ ገቢር ነበብ የፖለቲካ ኢኮኖሚ እይታ የተቃኘ የፖሊሲ ማዕቀፍ መከተል ከጀመረች ሰነባብታለች።

‎ይኅው አዲስ አቅጣጫ፤ ሀገሪቱ ለወቅታዊ የዓለምና የሀገር ውስጥ ነባራዊ ሁኔታዎች ምላሽ የሚሰጡ ተግባራዊ መፍትሄዎችን እንድትቀይስ አስችሏታል። በተለይም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሚመራው የሪፎርም ጉዞ፣ መንግሥትንና የግሉን ዘርፍ እንደ ወሳኝ አጋር በማየት፣ በውጤትና በውጤታማነት ላይ የተገነባ አዲስ የመንግሥት የሥራ ባህልን ተቋማዊ አድርጓል።

‎‎በዚህ ገቢር ነበብ እይታ አማካኝነት፣ በሚከተሉት ስምንት ቁልፍ ምሰሶዎች ወሳኝ ስኬቶች ተመዝግበዋል፦

‎• በኢኮኖሚ ዕይታ ረገድ፦ የመንግሥትን ሚና ዳግም በመተርጎም፣ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችና ዘርፈ-ብዙ የኢኮኖሚ አቅጣጫዎች አማካኝነት የገበያ ውድድር እንዲሰፍንና የኢኮኖሚ አቅም እንዲጎለብት ተደርጓል።

‎• በአማራጭ ፋይናንስ ዘርፍ፦ የካፒታል ገበያ ልማትን በማብሰር፣ የመንግሥትና የግል አጋርነትን በማጠናከር እና ዘመናዊ የገንዘብ ገበያ በመፍጠር የሀገሪቱን የፋይናንስ አማራጮች ማሳደግ ተችሏል።

‎• በኢኮኖሚ አመራር በኩል፦ በመደበኛ ክትትልና ግምገማ፣ በማክሮ ኮሚቴና በዘርፍ ካውንስሎች የተቀናጀ አሰራር አማካኝነት የገንዘብ ፖሊሲና የፕሮጀክቶች አስተዳደር ይበልጥ ውጤታማና ቀልጣፋ እንዲሆን ተደርጓል።

‎• የግል ዘርፍ ሚናን በማሳደግ፦ የግሉ ዘርፍ ከማህበራዊ ኃላፊነት ባለፈ የኢኮኖሚው መሪና ዋና ሞተር እንዲሆን በማድረግ እንደ ትልቅ የልማት አጋር እንዲሳተፍ ምቹ ሁኔታዎች ተፈጥረዋል።

‎• በልማት አጋርነትና ንግድ ትስስር ፦ የብድር ሽግሽግና አዲስ ፋይናንስን በማረጋገጥ፣ ለዓለም ንግድ ድርጅት (WTO) አባልነት የሚደረገውን ሂደት በማፋጠንና የAfCFTA ትግበራን ውጤታማ በማድረግ የሀገሪቱ ዓለም አቀፋዊ የንግድ ተወዳዳሪነት ከፍ ብሏል።

‎• በማህበራዊ ደህንነት ረገድ፦ አካታችነትን፣ ተደራሽነትንና ጥራትን መሠረት ያደረገ የሰው ተኮር ድጋፍ ሥርዓት በመዘርጋት፣ የማህበራዊ ጥበቃ አገልግሎቶች ዘላቂነት እንዲኖራቸው ማድረግ ተችሏል።

‎• በፍትሃዊ የመሰረተ ልማት ስርዓት ፦ የአካባቢ ጸጋን መሠረት ያደረገ፣ በግልጽ የሕግ ማዕቀፍ የሚመራና ያለፉ የፍትሃዊነት ክፍተቶችን የሚሞላ የመሰረተ ልማት ግንባታ ሥርዓት ተግባራዊ ሆኗል።

‎• በስርዓት ግንባታ በኩል፦ ብሔራዊ አካታች ምክክርን በማካሄድ፣ በፍትህና በሲቪል ሰርቪስ ዘርፎች ሪፎርም በማድረግ እንዲሁም የዲሞክራሲ ተቋማትን በማጠናከር ረገድ ጉልህ ውጤቶች ተመዝግበዋል።

#PMOEthiopia

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025