🔇Unmute
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በኢንዱስትሪው ዘርፍ የሚዘጋጁ ኤክስፖዎች የአምራች ኢንዱስትሪዎችን የማምረት ዐቅምና የእርስበርስ ትስስር በማጠናከር ተወዳዳሪነትን ለማላቅ መደላድል እየፈጠሩ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ገለጸ።
ድሬ ታምርት፤ ኢትዮጵያ ትበልጽግ በሚል መሪ ሐሳብ በድሬዳዋ የተዘጋጀ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ኤክስፖ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ተከፍቷል።

የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል በዚሁ ወቅት፤ ኤክስፖዎች የአምራች ኢንዱስትሪዎች የምርት ጥራትና ደረጃን በማሟላት ረገድ የደረሱበትን ከፍታ ለማሳየትና ለሚስተዋሉ ክፍተቶች ዘላቂ መፍትሔ ለመስጠት እያገዙ መሆኑን ተናግረዋል።

በተጨማሪም የእርስበርስ ትስስርን፣ መመጋገብንና ውድድርን በማጠናከር ሀገራዊ ትልምን ከዳር ለማድረስ ምቹ መደላድል እየፈጠሩ መሆኑን አስረድተዋል።
ከሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ሀገር አቀፍ ኤክስፖ እንደሚዘጋጅም ጠቁመዋል።
በኤክስፖው ላይ ምርታቸውን ያቀረቡ የአምራች ኢንዱስትሪ ተወካዮች በበኩላቸው፤ የግብዓት ልውውጥና የገበያ ትስስር ለመፍጠር ኤክስፖዎች መዘጋጀታቸው ለአምራች ኢንዱስትሪው ወሳኝ አበርክቶ እንዳላቸው ገልጸዋል።

ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎቹ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በተደረገላቸው ድጋፍ ወደ ማምረት የተሸጋገሩ አዳዲስ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ጎብኝተዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026