የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ያገኘነውን ልምድና እውቀት ተጠቅመን ማህበራት የተሻለ ቁመና ላይ እንዲደርሱ ኃላፊነታችንን እንወጣለን-ሰልጣኞች

Apr 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ኮምቦልቻ ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ያገኘነውን ልምድና እውቀት ተጠቅመን የሕብረት ሥራ ማህበራት የተሻለ ቁመና ላይ እንዲደርሱኃላፊነታችንን እንወጣለን ሲሉ በኮምቦልቻ የሕብረት ስራ ሪፎርም ስልጠና ተሳታፊዎች ገለፁ።

የኢትዮጵያ ሕብረት ሥራ ኮሚሽን “ቀበሌ የመድረስ ምዕራፍ” በሚል መሪ ሃሳብ በኮምቦልቻ ሲያካሄድ የቆየው 2ኛው ሀገር አቀፍ የሕብረት ሥራ ሪፎርም የንቅናቄ መድረክና ስልጠና ዛሬ ተጠናቋል።


የስልጠናው ተሳታፊዎች ፤ ከስልጠናው ያገኘነውን እውቀትና ልምድ ተጠቅመን የህብረት ስራ ማህበራት የተሻለ ቁመና ላይ ሆነው ኢኮኖሚውን እንዲያነቃቁ ኃላፊነታችንን እንወጣለን ብለዋል።

ከተሳታፊዎቹ መካከል አቶ ሰለሞን እንቁዬ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ኮሚሽኑ የጀመረው ሪፎርም ባለሙያውን በማነቃቃት ገበያውን እያረጋጋ ኢኮኖሚውንም እያሳደገ ይገኛል።


ስልጠናው ህብረት ስራ ማህበራትን ለማጠናከር፣ ለማዘመን፣ የፋይናንስ ስርዓቱን ለማሻሻል፣ የፈጠራ ስራዎችንና አዳዲስ ሀሳቦችን በማዋሀድ በሪፎርሙ የተገኘውን ውጤት ለማስቀጠልና ለማጠናከር ያግዛል ብለዋል።

በዚህም ያገኘነውን ልምድና እውቀት ተጠቅመን ማህበራት የተሻለ ቁመና ላይ እንዲደርሱና ኢኮኖሚውን እንዲያነቃቁ የድርሻችንን እንወጣለን ብለዋል።

ሌላኛዋ ሰልጣኝ ማርታ ጌቱ በበኩላቸው፣ ስልጠናው የህብረት ስራ ማህበራትን እንቅስቃሴ በማጎልበት ለውጤት እንዲበቃ ሚናው የጎላ መሆኑን አመልክተዋል።


በተለይ ማህበራትን በአዲስ በማደራጀት፣ በቴክኖሎጂ በማስደገፍ፣ ካፒታላቸውን በማሳደግና የቁጠባ ባህላቸውን በማጠናከር ገበያውን እንዲያረጋጉና ኢኮኖሚውን እንዲያነቃቁ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ገልጸዋል።

ማህበራት የተሻለ ቁመና ላይ እንዲደርሱ በተከናወኑ ተግባራት የተገኘውን አበረታት ውጤት አጠናክሮ ለማስቀጠል በቅንጅት እንሰራለን፣ ለዚህም ከስልጠናው እውቀትና ልምድ አግኝተናል ያሉት ደግሞ አቶ መሀመድ ሆላ ናቸው።


በተለይ ማህበራትን ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ጋር በማጣጣም የበለጠ ለውጤት እንዲበቁ የሚያስችል መሆኑን ጠቁመው በኮምቦልቻ ከተማ ተዘዋውረን በመጎብኘት የልምድ ለውውጥም ማድረግ ችለናል ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ህብረት ሥራ ኮሚሽን ጽህፈት ቤት ኃላፊና የስልጠናው አስተባባሪ አቶ አምባዬ ወልዴ በበኩላቸው፤ ህብረት ስራ ማህበራትን በማጠናከር፣ በማዘመን፣ ካፒታላቸውን በማሳደግ፣ ትስስር እንዲፈጥሩና የላቀ ደረጃ እንዲደርሱ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡


ለዚህም አዲስ ሪፎርም ተዘጋጅቶ ወደ ትግበራ መገባቱን አስታውሰው ኢኮኖሚውን በማነቃቃትና ገበያውን በማረጋጋት ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን ገልጸዋል።

የበለጠ ለማጠናከርና ባለሙያውንም ለማነቃቃት በተለያየ ዙር ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን ጠቁመው በኮምቦልቻ ሲካሄድ የቆየው ስልጠናም ዛሬ መጠናቀቁን ገልጸዋል።

ከሚያዚያ 13 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምሮ ሲካሄድ በቆየው ስልጠናና የንቅናቄ መድረክ የፌዴራል፣ የክልል፣ የዞንና የከተማ አመራሮች እንዲሁም የአማራና የአፋር ክልል የቀበሌ ህብረት ሥራ ማህበራት ባለሙያዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025