🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ የቻይና ባለሃብቶችን የንግድና ኢንቨስትመንት ተሳትፎ እያሳደገ መሆኑን በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቼን ሃይ ገለጹ።
አምባሳደር ቼን ሃይ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ኢትዮጵያ እና ቻይና ታሪካዊና ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ያላቸው ሀገራት ናቸው።
የኢትዮ-ቻይና ታሪካዊ ግንኙነት የልማት ትብብርን በማጎልበት የሀገራቱን ሁለንተናዊ ግንኙነት እያጠናከረ እንደሚገኝም ገልጸዋል።
የሀገራቱ የሁለትዮሽ የንግድና ኢንቨስትመንት ስትራቴጂክ አጋርነት ከፍተኛ ዕድገት በማስመዝገብ የጋራ ተጠቃሚነትን እያረጋገጠ መሆኑን ተናግረዋል።
የቻይና ባለሃብቶች በኢትዮጵያ የሚሰማሩባቸው አዳዲስ የንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፎችም ከፍተኛ ዕድገት እያስመዘገቡ መሆኑን አንስተዋል።
የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያም የቻይና አልሚ ባለሃብቶችን የኢንቨስትመንት በራስ መተማመን በማጎልበት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አስረድተዋል።
ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው የፈጠረው የኢትዮጵያ የንግድና ኢንቨስትመንት ከባቢም አዳዲስ ዕድሎችን መጠቀም የሚሹ በርካታ የቻይና ባለሀብቶችን እየሳበ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
የኢትዮ-ቻይና የኢኮኖሚ ትብብርም በግብርና፣ ኢንዱስትሪና የሰው ሃብት ልማት ሶስት ወሳኝ ምሰሶዎችን ማዕከል በማድረግ በስፋት እየተሰራበት መሆኑን አንስተዋል።
የኢትዮጵያ ፈጣን የልማትና የዕድገት አቅጣጫ የሀገራቱን ስትራቴጂክ አጋርነት በማጠናከር ከፍተኛ አቅም መፍጠሩን ገልጸዋል።
የቻይና ባለሃብቶች የኢትዮጵያ የንግድና የአምራች ኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት ተሳትፎም የኢኮኖሚ ልማትና ሽግግርን በማፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝም ተናግረዋል።
የሀገራቱ በሰው ሃብት ልማት ትብብር የአዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ በክህሎት የበለፀጉ ዜጎችን በማፍራት ወሳኝ ሚና እየተወጣ መሆኑን አስገንዝበዋል።
በሚቀጥሉት ዓመታትም የሀገራቱን የንግድና ኢንቨስትመንት ስትራቴጂክ አጋርነት የበለጠ በማጠናከር የሁለትዮሽ ግንኙነትን የበለጠ ለማጠናከር እንደሚሰራ ጠቅሰዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025