🔇Unmute
ጅማ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ለህዝብ ጥያቄዎች ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶችን በመገንባት የብልጽግና ጉዞን የማፋጠን ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነመራ ቡሊ ገለጹ።
በጅማ ዞን ኦሞ ናዳ ወረዳ በመንግስት እና በህዝብ ተሳትፎ የተገነቡ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል።

በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነመራ ቡሊ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ከዚህ ቀደም የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተጀምረው ሳይጠናቀቁ የመቅረት ችግር ነበር።
ባለፉት አምስት እና ስድስት ዓመታት ግን በርካታ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን መጀመር ብቻ ሳይሆን በስኬት ማጠናቀቅ ተችሏል ብለዋል።
ፕሮጀክቶች ለረጅም ዓመታት ሳይጠናቀቁ መቆየታቸው ህዝቡን ተስፋ ከማሳጣቱ ባለፈ ለከፍተኛ የሀብት ብክነት ምክንያት ሆኖ መቆየቱንም ጠቅሰዋል።
በአሁኑ ወቅት የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች በጥራትና በብዛት ተገንብተው ለአገልግሎት የሚበቁበት አዲስ የሥራ ባህል መፈጠሩንና ይህም የበለጠ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
"አሁን ላይ ፕሮጀክቶች በጥራት እና በብዛት እየተገነቡ የህዝቡም የልማት ጥያቄ እየተመለሰ ይገኛል'' ሲሉም ገልጸዋል።

የጅማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር በበኩላቸው፤ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የነዋሪዎችን የልማት እና የሰላም ጥያቄ ለመመለስ የተከናወኑ ተግባራት ትልቅ ውጤት ማስመዝገባቸውን ገልጸዋል።
ማህበረሰቡ ምቹ እና የተሟላ አገልግሎት ማግኘት እንደሚፈልግ የጠቀሱት አስተዳዳሪው፤ ይህንን ፍላጎት ለማርካት የሚያግዙ የወረዳ እና የከተማ አስተዳደር ህንፃዎች ተገንብተው መመረቃቸውን ተናግረዋል።
በቀጣይም ቀሪ ፕሮጀክቶችን በፍጥነት አጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት የማድረግ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
በዛሬው እለትም የኦሞ ናዳ ወረዳ አስተዳደር እና የከተማ አስተዳደር ህንፃዎች የተመረቁ ሲሆን፣ ከ120 ሚሊዮን ብር በላይ የግንባታ ወጪ መደረጉን ገልጸዋል።
የተመረቁ ፕሮጀክቶችም ለወረዳው ነዋሪዎች የተቀላጠፈና ምቹ አገልግሎት መስጠት የሚያስችሉ ናቸው ብለዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025