የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ ለህዝብ ጥያቄዎች ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶችን በመገንባት የብልጽግና ጉዞን የማፋጠን ስራ ይቀጥላል -አቶ ነመራ ቡሊ

May 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጅማ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ለህዝብ ጥያቄዎች ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶችን በመገንባት የብልጽግና ጉዞን የማፋጠን ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነመራ ቡሊ ገለጹ።

በጅማ ዞን ኦሞ ናዳ ወረዳ በመንግስት እና በህዝብ ተሳትፎ የተገነቡ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል።


በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነመራ ቡሊ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ከዚህ ቀደም የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተጀምረው ሳይጠናቀቁ የመቅረት ችግር ነበር።

ባለፉት አምስት እና ስድስት ዓመታት ግን በርካታ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን መጀመር ብቻ ሳይሆን በስኬት ማጠናቀቅ ተችሏል ብለዋል።

ፕሮጀክቶች ለረጅም ዓመታት ሳይጠናቀቁ መቆየታቸው ህዝቡን ተስፋ ከማሳጣቱ ባለፈ ለከፍተኛ የሀብት ብክነት ምክንያት ሆኖ መቆየቱንም ጠቅሰዋል።

በአሁኑ ወቅት የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች በጥራትና በብዛት ተገንብተው ለአገልግሎት የሚበቁበት አዲስ የሥራ ባህል መፈጠሩንና ይህም የበለጠ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

"አሁን ላይ ፕሮጀክቶች በጥራት እና በብዛት እየተገነቡ የህዝቡም የልማት ጥያቄ እየተመለሰ ይገኛል'' ሲሉም ገልጸዋል።


የጅማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር በበኩላቸው፤ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የነዋሪዎችን የልማት እና የሰላም ጥያቄ ለመመለስ የተከናወኑ ተግባራት ትልቅ ውጤት ማስመዝገባቸውን ገልጸዋል።

ማህበረሰቡ ምቹ እና የተሟላ አገልግሎት ማግኘት እንደሚፈልግ የጠቀሱት አስተዳዳሪው፤ ይህንን ፍላጎት ለማርካት የሚያግዙ የወረዳ እና የከተማ አስተዳደር ህንፃዎች ተገንብተው መመረቃቸውን ተናግረዋል።

በቀጣይም ቀሪ ፕሮጀክቶችን በፍጥነት አጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት የማድረግ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

በዛሬው እለትም የኦሞ ናዳ ወረዳ አስተዳደር እና የከተማ አስተዳደር ህንፃዎች የተመረቁ ሲሆን፣ ከ120 ሚሊዮን ብር በላይ የግንባታ ወጪ መደረጉን ገልጸዋል።

የተመረቁ ፕሮጀክቶችም ለወረዳው ነዋሪዎች የተቀላጠፈና ምቹ አገልግሎት መስጠት የሚያስችሉ ናቸው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉራጌ ዞን በፍራፍሬና ቅመማ ቅመም  ልማት የተሰማሩ አርሶ አደሮች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እያደገ ነው

ወልቂጤ ፤ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ በፍራፍሬ እና ቅመማ ቅመም ልማት ላይ መሰማራታችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ የጉራጌ ዞን አርሶ ...

Jul 29, 2026

አፍሪካ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ በመገንባት ዓለም አቀፍ ተደማጭነቷን ማጎልበት አለባት

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ በመገንባት ዓለም አቀፋዊ ተደማጭነቷንና ተጽዕኖ ፈጣሪነቷን ማጎልበ...

Jul 29, 2026

በክልሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ ይጠናከራል

ዲላ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ እንደሚጠ...

Jul 16, 2026

የሩዝ ልማት ምርታማነትን በማሳደግ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ አድርጓል

መቱ ፤ ሐምሌ 2/ 2018(ኢዜአ):- የሩዝ ልማት ስራ ላይ መሳተፋችን ምርታማነትን በማሳደግ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ በኢሉባቦር ዞ...

Jul 10, 2026