የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ ለህዝብ ጥያቄዎች ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶችን በመገንባት የብልጽግና ጉዞን የማፋጠን ስራ ይቀጥላል -አቶ ነመራ ቡሊ

May 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጅማ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ለህዝብ ጥያቄዎች ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶችን በመገንባት የብልጽግና ጉዞን የማፋጠን ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነመራ ቡሊ ገለጹ።

በጅማ ዞን ኦሞ ናዳ ወረዳ በመንግስት እና በህዝብ ተሳትፎ የተገነቡ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል።


በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነመራ ቡሊ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ከዚህ ቀደም የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተጀምረው ሳይጠናቀቁ የመቅረት ችግር ነበር።

ባለፉት አምስት እና ስድስት ዓመታት ግን በርካታ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን መጀመር ብቻ ሳይሆን በስኬት ማጠናቀቅ ተችሏል ብለዋል።

ፕሮጀክቶች ለረጅም ዓመታት ሳይጠናቀቁ መቆየታቸው ህዝቡን ተስፋ ከማሳጣቱ ባለፈ ለከፍተኛ የሀብት ብክነት ምክንያት ሆኖ መቆየቱንም ጠቅሰዋል።

በአሁኑ ወቅት የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች በጥራትና በብዛት ተገንብተው ለአገልግሎት የሚበቁበት አዲስ የሥራ ባህል መፈጠሩንና ይህም የበለጠ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

"አሁን ላይ ፕሮጀክቶች በጥራት እና በብዛት እየተገነቡ የህዝቡም የልማት ጥያቄ እየተመለሰ ይገኛል'' ሲሉም ገልጸዋል።


የጅማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር በበኩላቸው፤ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የነዋሪዎችን የልማት እና የሰላም ጥያቄ ለመመለስ የተከናወኑ ተግባራት ትልቅ ውጤት ማስመዝገባቸውን ገልጸዋል።

ማህበረሰቡ ምቹ እና የተሟላ አገልግሎት ማግኘት እንደሚፈልግ የጠቀሱት አስተዳዳሪው፤ ይህንን ፍላጎት ለማርካት የሚያግዙ የወረዳ እና የከተማ አስተዳደር ህንፃዎች ተገንብተው መመረቃቸውን ተናግረዋል።

በቀጣይም ቀሪ ፕሮጀክቶችን በፍጥነት አጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት የማድረግ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

በዛሬው እለትም የኦሞ ናዳ ወረዳ አስተዳደር እና የከተማ አስተዳደር ህንፃዎች የተመረቁ ሲሆን፣ ከ120 ሚሊዮን ብር በላይ የግንባታ ወጪ መደረጉን ገልጸዋል።

የተመረቁ ፕሮጀክቶችም ለወረዳው ነዋሪዎች የተቀላጠፈና ምቹ አገልግሎት መስጠት የሚያስችሉ ናቸው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026