የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በምግብና መጠጥ ማቀነባበር የተሰማሩ ኢንዱስትሪዎች ህብረተሰቡ በንጥረ ነገር የበለፀጉ ምርቶችን እንዲያገኝ እያደረጉ ነው

May 26, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 17/2018(ኢዜአ)፦ በግብርና ምርት የምግብና መጠጥ ማቀነባበር የተሰማሩ ኢንዱስትሪዎች ህብረተሰቡ በንጥረ ነገር የበለፀጉ ምርቶችን እንዲያገኝ እያደረጉ መሆናቸውን የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ገለጸ።

በአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት የምግብና መጠጥ ኢንዱስትሪ ምርምርና ልማት ማዕከል ከቴክኖ-ሰርቭ ጋር በመተባበር የበለፀገ የስንዴ ዱቄትና የምግብ ዘይት የገበያ ትስስር ፎረም በአዲስ አበባ አካሂዷል።


የማዕከሉ ዋና ሥራ አስኪያጅ ደበበ ወርቁ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በምግብ ዘርፍ የስንዴና የማሽላ ዱቄት የጨውና የዘይት ምርቶች አስገዳጅ ደረጃ ወጥቶላቸዋል።

በዚህም አምራች ኢንዱስትሪዎች የበለፀገ የምግብ ምርት ዝግጅት ሰርተፊኬት በመውሰድ ጥራትና ደረጃቸውን የጠበቁ ምርቶችን ለገበያ የሚያቀርቡበትን የቴክኒክ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

የምግብ ምርት አምራቾችም በተለያዩ ንጥረ ነገሮች የበለፀጉ ምርቶችን ለማህበረሰቡ በማቅረብ ከፍተኛ እገዛ እያደረጉ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በግብርና ምርት ማቀነባበሪያ ፋብሪካ በንጥረ ነገር በለፀገ የምግብ ምርታማነት አቅም ጤናማና አምራች ዜጋን በማፍራት ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን ለመተካት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳላቸው አንስተዋል።

በቀጣይም በበለፀገ የምግብ ምርት ማቀነባበር ለተሰማሩ ኢንዱስትሪዎች ድጋፍ በማድረግ የምርት ጥራትና አቅማቸውን እንዲያሳደጉ ድጋፍ እንደሚደረግ አረጋግጠዋል።


በቴክኖ ሰርቭ ተቋም የሚለር ፎር ኒውትሬሽን ፕሮግራም ማናጀር ገረመው ጣሰው በበኩላቸው፤ አምራቾች የተሳለጠ የምግብ ማበልፀግ ሥራ እንዲያከናውኑ የቴክኒክ ድጋፍ እየተደረገ ነው ብለዋል።

በቀጣይም በበለፀገ የምግብ ማቀነባበርና ዝግጅት ለተሰማሩ ድርጅቶች የሚያደርገውን አተዋጽኦ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

የዋኬኒ ምግብ ፋብሪካ ፕሮዳክሽን ማናጀር አማኑዔል ታደሰ፤ መንግስት ለፋብሪካዎች የሰጠው ልዩ ትኩረት ምርቶቻችንን በጥራትና በስፋት ተደራሽ እንድናደርግ አስችሎናል ብለዋል።

ሌላኛው የዲና ምግብ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ የሽያጭና ስርጭት ሥራ አስኪያጅ እንየው ጫኔ በበኩሉ፤ ኢትዮጵያ ታምርትን ጨምሮ መንግስት ዘርፉን ለማሳደግ የሚያደርገው ድጋፍ እያደገ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026