የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ ሰላምን በማጽናት የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን በቅንጅት ማሳካት ተችሏል - ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

May 28, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደሴ፤ ግንቦት 18/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ሰላምን በማጽናት የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን በቅንጅት ማሳካት መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለፁ።

በደሴ ከተማ አስተዳደር በ1 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር የተገነቡ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ዛሬ ተመርቀዋል።

የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በምረቃው ወቅት እንደገለፁት፤ የክልሉን ሰላም በማጽናት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ሰፋፊ የልማት ፕሮጀክቶችን በመገንባት ለውጤት እንዲበቁ ተደርጓል።


የልማት ፕሮጀክቶቹን በቅንጅት በማሳካት የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በየደረጃው ለመመለስ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል።

የህዝቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመመለስ፣ የገበያ መረጋጋትን ለማምጣት፣ የስራ እድልን ለመፍጠር፣ የትምህርትና የጤናው ዘርፍ ተደራሽነትን ለማሳደግ እየተደረጉ ያሉ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።

የክልሉን እድገት በማረጋገጥ ወደ ሁለተናዊ ብልጽግና የማሸጋገር ተግባራት በቅንጅት እንደሚከናወኑ ጠቁመው በደሴ ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የኮሪደር ልማት፣ የአስፋልት መንገድና ሌሎች የመሰረት ልማት ግንባታዎች ይጠናከራሉ ብለዋል።

የደሴ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ሳሙኤል ሞላልኝ በበኩላቸው የከተማውን ሰላምና ልማት ዘላቂ ለማድረግ ህብረተሰቡን ያሳተፉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ጠቁመዋል።


በዚህም በከተማው የአስፋልት መንገድ፣ የኮሪደር ልማት፣ የመናኸሪያ፣ የፍሳሽ ማስወገጃ፣ የንጹህ መጠጥ ውሃ፣ የትምህርት ቤት ማስፋፊያና ሌሎች መሰረተ ልማቶች ተጠናቅቀው ዛሬ ለምርቃ በቅተዋል ብለዋል።

የልማት ስራዎቹ መንግስት ለሰው ተኮር ፕሮጀክቶች በሰጠው ትኩረት የተከናወኑ መሆናቸውን ገልጸው የማህበረሰቡን ተጠቃሚነትም አሳድገዋል ነው ያሉት።

በምረቃ መርሃ ግብሩ የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንቱ ተስፋዬ፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር)ን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026