🔇Unmute
ደሴ፤ ግንቦት 18/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ሰላምን በማጽናት የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን በቅንጅት ማሳካት መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለፁ።
በደሴ ከተማ አስተዳደር በ1 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር የተገነቡ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ዛሬ ተመርቀዋል።
የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በምረቃው ወቅት እንደገለፁት፤ የክልሉን ሰላም በማጽናት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ሰፋፊ የልማት ፕሮጀክቶችን በመገንባት ለውጤት እንዲበቁ ተደርጓል።

የልማት ፕሮጀክቶቹን በቅንጅት በማሳካት የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በየደረጃው ለመመለስ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል።
የህዝቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመመለስ፣ የገበያ መረጋጋትን ለማምጣት፣ የስራ እድልን ለመፍጠር፣ የትምህርትና የጤናው ዘርፍ ተደራሽነትን ለማሳደግ እየተደረጉ ያሉ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
የክልሉን እድገት በማረጋገጥ ወደ ሁለተናዊ ብልጽግና የማሸጋገር ተግባራት በቅንጅት እንደሚከናወኑ ጠቁመው በደሴ ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የኮሪደር ልማት፣ የአስፋልት መንገድና ሌሎች የመሰረት ልማት ግንባታዎች ይጠናከራሉ ብለዋል።
የደሴ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ሳሙኤል ሞላልኝ በበኩላቸው የከተማውን ሰላምና ልማት ዘላቂ ለማድረግ ህብረተሰቡን ያሳተፉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

በዚህም በከተማው የአስፋልት መንገድ፣ የኮሪደር ልማት፣ የመናኸሪያ፣ የፍሳሽ ማስወገጃ፣ የንጹህ መጠጥ ውሃ፣ የትምህርት ቤት ማስፋፊያና ሌሎች መሰረተ ልማቶች ተጠናቅቀው ዛሬ ለምርቃ በቅተዋል ብለዋል።
የልማት ስራዎቹ መንግስት ለሰው ተኮር ፕሮጀክቶች በሰጠው ትኩረት የተከናወኑ መሆናቸውን ገልጸው የማህበረሰቡን ተጠቃሚነትም አሳድገዋል ነው ያሉት።
በምረቃ መርሃ ግብሩ የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንቱ ተስፋዬ፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር)ን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026