የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመንግሥት አገልግሎቶችን በማዘመን የዜጎችን እንግልት እያስቀረ ነው

Jun 5, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 27/2018(ኢዜአ)፦መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመንግሥት አገልግሎቶችን በማዘመን የዜጎችን እንግልት እያስቀረ መሆኑን የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

ከንቲባዋ በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ የተገነባውን መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት መርቀው ከፍተዋል።


ከንቲባ አዳነች አቤቤ በምረቃ ሥነ-ስርዓቱ እንደገለጹት፤ በአዲስ አበባ የመንግሥት አገልግሎቶችን ፍትሀዊነት የሚያረጋግጥ ቀልጣፋና ፈጣን የአገልግሎት አሰጣጥ ምኅዳር እየተፈጠረ ነው።

የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ህብረተሰቡ የመንግሥት አገልግሎቶችን ለማግኘት የሚያጋጥመውን የመልካም አስተዳደር ችግር በማስቀረት አዎንታዊ ሚና እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል።

የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎትንም ከአንድ ማዕከል ወደ ተንቀሳቃሽ በማሸጋገር የተደራሽነት አድማሱን የማስፋት ሥራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።


ይህም ከተማ አስተዳደሩ የአዲስ አበባን የመንግሥት አገልግሎቶች ቀልጣፋና ውጤታማ ለማድረግ የወሰደውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ አስረድተዋል።

ለምረቃ የበቃው የኮልፌ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ለህብረተሰቡ ዘመናዊና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት በሚያስችል መልኩ የተገነባ መሆኑን አብራርተዋል።

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ ኃላፊ ጀማሉ ጀንበር (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የዜጎችን እንግልት እያስቀረ ያለ ውጤታማ ስራ ነው ብለዋል።


በዚህም በመዲናዋ የመሶብ አንድ ማዕከላት ተደራሽነትን በማስፋትና የመንግሥት አገልግሎቶችን በማዘመን የመፈፀም ውጤታማነትን እያሻሻለ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ቴዎድሮስ ወልደ ሚካኤል፤ የኮልፌ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የክፍለ ከተማውን አገልግሎቶች ለማሳለጥ ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026