የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመንግሥት አገልግሎቶችን በማዘመን የዜጎችን እንግልት እያስቀረ ነው

Jun 5, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 27/2018(ኢዜአ)፦መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመንግሥት አገልግሎቶችን በማዘመን የዜጎችን እንግልት እያስቀረ መሆኑን የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

ከንቲባዋ በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ የተገነባውን መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት መርቀው ከፍተዋል።


ከንቲባ አዳነች አቤቤ በምረቃ ሥነ-ስርዓቱ እንደገለጹት፤ በአዲስ አበባ የመንግሥት አገልግሎቶችን ፍትሀዊነት የሚያረጋግጥ ቀልጣፋና ፈጣን የአገልግሎት አሰጣጥ ምኅዳር እየተፈጠረ ነው።

የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ህብረተሰቡ የመንግሥት አገልግሎቶችን ለማግኘት የሚያጋጥመውን የመልካም አስተዳደር ችግር በማስቀረት አዎንታዊ ሚና እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል።

የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎትንም ከአንድ ማዕከል ወደ ተንቀሳቃሽ በማሸጋገር የተደራሽነት አድማሱን የማስፋት ሥራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።


ይህም ከተማ አስተዳደሩ የአዲስ አበባን የመንግሥት አገልግሎቶች ቀልጣፋና ውጤታማ ለማድረግ የወሰደውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ አስረድተዋል።

ለምረቃ የበቃው የኮልፌ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ለህብረተሰቡ ዘመናዊና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት በሚያስችል መልኩ የተገነባ መሆኑን አብራርተዋል።

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ ኃላፊ ጀማሉ ጀንበር (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የዜጎችን እንግልት እያስቀረ ያለ ውጤታማ ስራ ነው ብለዋል።


በዚህም በመዲናዋ የመሶብ አንድ ማዕከላት ተደራሽነትን በማስፋትና የመንግሥት አገልግሎቶችን በማዘመን የመፈፀም ውጤታማነትን እያሻሻለ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ቴዎድሮስ ወልደ ሚካኤል፤ የኮልፌ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የክፍለ ከተማውን አገልግሎቶች ለማሳለጥ ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉራጌ ዞን በፍራፍሬና ቅመማ ቅመም  ልማት የተሰማሩ አርሶ አደሮች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እያደገ ነው

ወልቂጤ ፤ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ በፍራፍሬ እና ቅመማ ቅመም ልማት ላይ መሰማራታችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ የጉራጌ ዞን አርሶ ...

Jul 29, 2026

አፍሪካ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ በመገንባት ዓለም አቀፍ ተደማጭነቷን ማጎልበት አለባት

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ በመገንባት ዓለም አቀፋዊ ተደማጭነቷንና ተጽዕኖ ፈጣሪነቷን ማጎልበ...

Jul 29, 2026

በክልሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ ይጠናከራል

ዲላ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ እንደሚጠ...

Jul 16, 2026

የሩዝ ልማት ምርታማነትን በማሳደግ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ አድርጓል

መቱ ፤ ሐምሌ 2/ 2018(ኢዜአ):- የሩዝ ልማት ስራ ላይ መሳተፋችን ምርታማነትን በማሳደግ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ በኢሉባቦር ዞ...

Jul 10, 2026