የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በኦሮሚያ ክልል በዚህ ዓመት 16 ነጥብ 9 ሚሊዮን ኩንታል ቡና ተመርቷል

Jun 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦ በኦሮሚያ ክልል በተጠናቀቀው የምርት ዘመን 16 ነጥብ 9 ሚሊዮን ኩንታል አጠቃላይ የቡና ምርት መገኘቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

በቢሮው የቡና ጥራት እና ልማት ዳይሬክተር አቶ ታከለ ኃይለማርያም ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ በክልሉ የቡና ልማት በልዩ ኢንሼቲቭ ተቀርጾ ወደ ስራ ከገባ ወዲህ፣ የቡና ምርትና ምርታማነት በከፍተኛ ደረጃ እያደገ መጥቷል።

የአርሶ አደሩ ህይወትና ኑሮ ከቡና ልማት ጋር በቀጥታ የተሳሰረ መሆኑን የጠቀሱት ዳይሬክተሩ፤ የቡና ልማቱ በስፋትና በዘመናዊ መልኩ መከናወኑ የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን ገልጸዋል።

ቢሮው የቡና ምርትን በዓይነትና በብዛት ለማሳደግ በርካታ ስራዎችን ተግባራዊ ማድረጉን ጠቁመዋል።

ከእነዚህም መካከል በአጭር ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ የተሻሻሉ የቡና ችግኞችን ለአርሶ አደሩ ማድረስ፣ ያረጁና ምርት የማይሰጡ የቡና ተክሎችን በአዲስ የመተካት ዋና ዋናዎቹ ናቸው ብለዋል።

በተጨማሪም በግብርና ባለሙያዎች በመታገዝ የቡና ተክሎችን የመጎንደል ስራን በስፋት ማከናወን መቻሉንም ገልጸዋል።

በዚህም በክልሉ በ2018 የምርት ዘመን 18 ሚሊዮን ኩንታል የቡና ምርትን ለመሰብሰብ ታቅዶ፣ በእስካሁኑ ሂደት 16 ነጥብ 9 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ማግኘት ተችሏል ብለዋል።

ቡና በዓለም ገበያ ያለውን ተወዳዳሪነትና ጥራት ለማስጠበቅ አርሶ አደሩን ማዕከል ያደረጉ ተከታታይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች መሰራታቸውን አቶ ታከለ አብራርተዋል።

በተለይም አርሶ አደሮች የደረሰ ቀይ ቡና ብቻ እንዲለቅሙ ማድረግ የተቻለ መሆኑን የገለጹ ሲሆን የተሰበሰበውን ቡና በጥራት የማድረቅ ባህል ማደጉን ተናግረዋል።

የአርሶ አደሩን የምርት ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማሳደግና ህገ-ወጥ ደላሎችን ለመከላከል፣ ምርቱን ያለማንም ጣልቃ ገብነት በቀጥታ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች እየተፈጠሩ መሆናቸውን ኃላፊው አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026