የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በበጀት ዓመቱ 158 መካከለኛና ከፍተኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደማምረት ገብተዋል-ቢሮው

Jun 8, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ኮምቦልቻ፤ግንቦት 30/2018 (ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በበጀት ዓመቱ 158 መካከለኛ እና ከፍተኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች በአዲስ መልክ ማምረት መጀመራቸው ተገለጸ።

የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል እንዲሁም ሌሎች የፌዴራልና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ክልላዊ የማጠቃለያ መርሃግብር በኮምቦልቻ ከተማ እየተካሄደ ነው።


የአማራ ክልል ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ተፈሪ ታረቀኝ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በክልሉ በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ የነበሩ ችግሮችን እየፈታ መጥቷል።

በተለይም ባለሃብቱ ያነሳቸው የነበሩ የማስፋፊያና የአዳዲስ ኢንቨስትመንት ቦታዎች ጥያቄን፣ የብድርና የመሰረተ ልማት ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ ለመፍታት ማስቻሉን በማሳያነት ጠቅሰዋል።

ይህም የአምራች ኢንዱስትሪዎችን ከማስፋፋት ባሻገር የማምረት አቅማቸውን በማሳደግ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ለማስፋት እያገዘ መሆኑን ነው ያስረዱት።

በተያዘው በጀት ዓመት ባለፉት ወራት ብቻ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄው 158 መካከለኛና ከፍተኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች በአዲስ መልክ ማምረት መጀመራቸውንም ተናግረዋል።

የፌደራልና የክልሉ አመራሮቹ የተለያዩ የኢንዱስትሪ ምርቶችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን በቀጣይም ከባለሀብቶች ጋር ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

"ኢትዮጵያ ታምርት ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት" በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ ባለው በዚህ መርሃግብር ላይ 145 ኢንዱስትሪዎች ምርትና አገልግሎታቸውን እያስተዋወቁ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026