🔇Unmute
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የሌማት ትሩፋት መርሀ ግብር ለማር ምርት እድገት አስተዋጾ ማድረጉ ተገለጸ።
በክልሉ ባለፉት አስር ወራት 33 ሺህ ቶን ማር መመረቱ ተመላክቷል።
የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት ቢሮ የንብና ሀር ልማት ባለሙያ አቶ ሙሀመድ ጌታሁን ለኢዜአ እንደገለጹት፣ በክልሉ እየተተገበረ የሚገኘው የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ለማር ምርት እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል።
በመርሃ ግብሩ ትኩረት ሰጥቶ ከሚሰራባቸው ዘርፎች አንዱ የንብ ማነብ መሆኑን ጠቁመው በዘርፉ ከ500 ሺህ በላይ አባወራዎች፣ የተደራጁ ወጣቶችና ሴቶች እየተሳተፉ መሆኑን ተናግረዋል ።
በበጀት አመቱ አስር ወራት የንብ መንጋ ከያዙ 1 ነጥብ 9 ሚሊዮን ዘመናዊ፣ የሽግግርና ባህላዊ ቀፎዎች 33 ሺህ ቶን ማር መገኘቱን አስታውቀዋል።
የተገኘው የማር ምርት በበጀት አመቱ ለማምረት ከታቀው በላይ መሆኑን ጠቁመዋል ።
የሌማት ትሩፋት መርሀ ግብር ትግበራ ለንብ ማነብ የፈጠረው ምቹ ሁኔታ ለማር ምርት እድገት አስተዋጾ ማድረጉን አመልክተዋል።
በዘርፉ የገበያ ትስስር በመፍጠር የአናቢዎችን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው ብለዋል።
በዋግ ኽምኸራ ብሔረሰብ አስተዳደር በደሀና ወረዳ ቀበሌ 01 ነዋሪ አርሶ አደር አለባቸው በላይ እንዳሉት፣ በ21 ዘመናዊና በ26 ባህላዊ ቀፎዎች በመታገዝ በንብ ማነብ ስራ ተሰማርተዋል።
ዘንድሮ 410 ኪሎ ግራም ማር አምርተው በመሸጥ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በምስራቅ ጎጃም ዞን በሸበል በረንታ ወረዳ የመዝን ኪሮስ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ላቃቸው ደግዋለ በበኩላቸው በ42 ዘመናዊና ባህላዊ ቀፎዎች የንብ ማነብ ስራ እያከናወኑ መሆኑን አመልክተዋል።
ዘንድሮ እስካሁን ያመረቱን ከ170 ኪሎ ግራም በላይ ማር ለገበያ በማቅረብ ተጨማሪ ገቢ ማግኘታቸውን ገልጸዋል።
ወልቂጤ ፤ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ በፍራፍሬ እና ቅመማ ቅመም ልማት ላይ መሰማራታችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ የጉራጌ ዞን አርሶ ...
Jul 29, 2026
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ በመገንባት ዓለም አቀፋዊ ተደማጭነቷንና ተጽዕኖ ፈጣሪነቷን ማጎልበ...
Jul 29, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ እንደሚጠ...
Jul 16, 2026
መቱ ፤ ሐምሌ 2/ 2018(ኢዜአ):- የሩዝ ልማት ስራ ላይ መሳተፋችን ምርታማነትን በማሳደግ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ በኢሉባቦር ዞ...
Jul 10, 2026