የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በተደመረ አቅም የግብርና ምርታማነትን በማስፋትና በማሳደግ ከተረጂነት የመውጣት ጥረት በልዩ ትኩረት እየተሰራበት ነው- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

Jun 25, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ዱራሜ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦ በተደመረ አቅም የግብርና ምርታማነትን በማስፋትና በማሳደግ ከተረጂነት የመውጣት ጥረት በልዩ ትኩረት እየተሰራበት መሆኑን የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ።

"የተቀናጀ የግብርና ትጋት ለላቀ ምርታማነት" በሚል መሪ ሀሳብ የመኸር ወቅት የተቀናጀ የግብርና ልማት ስራዎች የንቅናቄ መድረክ በዱራሜ ከተማ ተካሄዷል።


ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ በክልሉ ከተረጂነት ለመውጣት እየተደረገ ያለውን ጥረት የሚያግዙ የግብርናው ዘርፍ የልማት ስራዎች ይጠናከራሉ።

በክልሉ በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ በሚገኙ ስራዎች ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ጠቁመው፤ በዚህም የማህበረሰቡ ተጠቃሚነት እያደገ ስለመምጣቱም አስረድተዋል።

የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ትግበራም የኑሮ ውድነትን በማረጋጋት ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማበርከት ላይ ይገኛል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ ተግባሩን ማላቅ እንደሚገባም ጠቁመዋል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር በበኩላቸው በክልሉ በ2018/19 የመኸር ወቅት 800 ሺህ ሄክታር የሚጠጋ ማሳ ይለማል ብለዋል።


በዚህም 70 ሚሊዮን ኩንታል የሚጠጋ ምርት ለማምረት ግብ ተቀምጦ ወደ ስራ መገባቱን ጠቁመዋል።

ክልሉ የግብርናውን ዘርፍ በማዘመን ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ እያከናወናቸው በሚገኙ ስራዎች ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በተለይም የአካባቢን ፀጋ ለይቶ በማልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመረው እሳቤ እውን በማድረግ የማህበረሰቡ ተጠቃሚነት እያደገ ስለመምጣቱም ጠቁመዋል።

በዚህም አርሶ አደሩ ከቤት ፍጆታው አልፎ ለገበያና ለኢንዱስትሪ ግብዓት የሚሆኑ ምርቶችን ማምረት ስለመጀመሩና ተግባሩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አመልክተዋል።

የንቅናቄ መድረኩ በመኸር ወቅት የታቀደውን ግብ ለማሳካት የጋራ ተግባቦት ለመፍጠር እንደሚያግዝና አመራሩና የግብርና ባለሙያው ለእቅዱ መሳካት የበኩሉን አስተዋጽኦ ሊያበረክት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አረጋ እሸቱ በበኩላቸው በዞኑ የመኸር ወቅት የግብርና ልማት 47 ሺህ ሄክታር ማሳ ስንዴንና ገብስን ጨምሮ በሌሎች ዋና ዋና ሰብሎች ይለማል ብለዋል።

በዞኑ የኩታ ገጠም እርሻ ትግበራ ለምርታማነት ማደግ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ጠቅሰው በመኸር ወቅት የግብርና ልማትም ስነ-ዘዴው በትኩረት ተግባራዊ እንደሚደረግም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግባር ይጠናከራል-ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

ሚዛን አማን፣ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግ...

Jun 25, 2026

ፋውንዴሽኑ ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመቀናጀት ለስራ ፈጣሪ ወጣቶች ድጋፍ እያደረገ ነው

ጂንካ፤ሰኔ 15/2018(ኢዜአ) ፡-የኃይለማርያምና ሮማን ፋውንዴሽን ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመቀናጀት በሚያደርግላቸው ድጋፍ ተጠቃሚ መሆናቸውን በደቡብ ኦሞ እና...

Jun 23, 2026

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026