የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በተደመረ አቅም የግብርና ምርታማነትን በማስፋትና በማሳደግ ከተረጂነት የመውጣት ጥረት በልዩ ትኩረት እየተሰራበት ነው- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

Jun 25, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ዱራሜ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦ በተደመረ አቅም የግብርና ምርታማነትን በማስፋትና በማሳደግ ከተረጂነት የመውጣት ጥረት በልዩ ትኩረት እየተሰራበት መሆኑን የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ።

"የተቀናጀ የግብርና ትጋት ለላቀ ምርታማነት" በሚል መሪ ሀሳብ የመኸር ወቅት የተቀናጀ የግብርና ልማት ስራዎች የንቅናቄ መድረክ በዱራሜ ከተማ ተካሄዷል።


ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ በክልሉ ከተረጂነት ለመውጣት እየተደረገ ያለውን ጥረት የሚያግዙ የግብርናው ዘርፍ የልማት ስራዎች ይጠናከራሉ።

በክልሉ በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ በሚገኙ ስራዎች ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ጠቁመው፤ በዚህም የማህበረሰቡ ተጠቃሚነት እያደገ ስለመምጣቱም አስረድተዋል።

የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ትግበራም የኑሮ ውድነትን በማረጋጋት ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማበርከት ላይ ይገኛል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ ተግባሩን ማላቅ እንደሚገባም ጠቁመዋል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር በበኩላቸው በክልሉ በ2018/19 የመኸር ወቅት 800 ሺህ ሄክታር የሚጠጋ ማሳ ይለማል ብለዋል።


በዚህም 70 ሚሊዮን ኩንታል የሚጠጋ ምርት ለማምረት ግብ ተቀምጦ ወደ ስራ መገባቱን ጠቁመዋል።

ክልሉ የግብርናውን ዘርፍ በማዘመን ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ እያከናወናቸው በሚገኙ ስራዎች ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በተለይም የአካባቢን ፀጋ ለይቶ በማልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመረው እሳቤ እውን በማድረግ የማህበረሰቡ ተጠቃሚነት እያደገ ስለመምጣቱም ጠቁመዋል።

በዚህም አርሶ አደሩ ከቤት ፍጆታው አልፎ ለገበያና ለኢንዱስትሪ ግብዓት የሚሆኑ ምርቶችን ማምረት ስለመጀመሩና ተግባሩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አመልክተዋል።

የንቅናቄ መድረኩ በመኸር ወቅት የታቀደውን ግብ ለማሳካት የጋራ ተግባቦት ለመፍጠር እንደሚያግዝና አመራሩና የግብርና ባለሙያው ለእቅዱ መሳካት የበኩሉን አስተዋጽኦ ሊያበረክት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አረጋ እሸቱ በበኩላቸው በዞኑ የመኸር ወቅት የግብርና ልማት 47 ሺህ ሄክታር ማሳ ስንዴንና ገብስን ጨምሮ በሌሎች ዋና ዋና ሰብሎች ይለማል ብለዋል።

በዞኑ የኩታ ገጠም እርሻ ትግበራ ለምርታማነት ማደግ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ጠቅሰው በመኸር ወቅት የግብርና ልማትም ስነ-ዘዴው በትኩረት ተግባራዊ እንደሚደረግም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026