የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ምሩቃን የዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም በተለያዩ ዘርፎች ስራ ፈጥረው ኢኮኖሚውን ሊደግፉ ይገባል

Jun 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደሴ ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ ተመራቂዎች የዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም በተለያዩ ዘርፎች ስራ ፈጥረው ኢኮኖሚውን ሊደግፉ እንደሚገባ የወሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት አወል ሰይድ (ዶ/ር) ገለፁ።

የወሎ ዩኒቨርሲቲ በተለያየ መርሃ ግብር በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን 843 ተማሪዎች ዛሬ አስመርቋል።


የወሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት አወል ሰይድ (ዶ/ር)፤ ምሩቃን ተማሪዎች የተለያዩ ውጣ ውረዶችን አልፈው ለዛሬ ምርቃት በመብቃታቸው እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።

በቆይታቸው ያገኙትን እውቀት፣ ልምድና ክህሎት ተጠቅመው ሀገርና ህዝባቸውን በእኩልነት፣ በታማኝነትና በቅንነት ሊያገለግሉ ይገባል ብለዋል።

ምሩቃን ስራ ፈጣሪ እንጅ ስራ ፈላጊ እንዳይሆኑ ያሳሰቡት ፕሬዚዳንቱ፣ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ተጠቅመው በተለያዩ ዘርፎች ስራ ሊፈጥሩና ኢኮኖሚውን ሊደግፉ ይገባል ብለዋል።

በሚሄዱበት አካባቢና በሚያገኙት አጋጣሚ ሁሉ ለኢትዮጵያ አንድነትና ሰላም እንዲሰሩም አመልክተዋል።

የእለቱ የክብር እንግዳና የደሴ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ሽመልስ ጌታቸው በበኩላቸው፣ ምሩቃን በቆይታቸው ያገኙትን ልምድና ክህሎት ወደ ተግባር በመቀየር ህዝብና ሀገር ሊያገለግሉ ይገባል ብለዋል።


የዛሬው ምርቃት የድል መጀመሪያ እንጅ መጨረሻ አለመሆኑን ተረድተው በቀጣይም እውቀትና ክህሎታቸውን በማሳደግ ለዲጂታል ኢትዮጵያ ትግበራ ስኬት የድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።

ታላቅ ህልምና ራዕይ ሰንቀው፣ ስነ ምግባራቸውን ጠብቀው፣ በታማኝነት የህብረተሰብ አገልጋይ እንዲሆኑም መክረዋል።

ተመራቂዎች ችግርና ፈተናዎችንም ወደ እድል በመቀየር የጀመሩትን የስኬት ጉዞ ሊቀጥሉ እንደሚገባ አመልክተው የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።


በእንሰሳት ህክምና ተመራቂዎች መካከል ተመስገን አሊ በሰጠው አስተያየት፤ በቆይታው ያገኘውን እውቀትና ክህሎት ተጠቅሞ በታማኝነት ለማገልገል ዝግጁ መሆኑን ገልጿል።

በመርሃ ግብሩ ላይም የደሴ ከተማና የወሎ ዩኒቨርሲቲ አመራሮች፣ የተማሪ ወላጆችና ቤተሰቦችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግባር ይጠናከራል-ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

ሚዛን አማን፣ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግ...

Jun 25, 2026

ፋውንዴሽኑ ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመቀናጀት ለስራ ፈጣሪ ወጣቶች ድጋፍ እያደረገ ነው

ጂንካ፤ሰኔ 15/2018(ኢዜአ) ፡-የኃይለማርያምና ሮማን ፋውንዴሽን ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመቀናጀት በሚያደርግላቸው ድጋፍ ተጠቃሚ መሆናቸውን በደቡብ ኦሞ እና...

Jun 23, 2026

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026