🔇Unmute
ደሴ ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ ተመራቂዎች የዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም በተለያዩ ዘርፎች ስራ ፈጥረው ኢኮኖሚውን ሊደግፉ እንደሚገባ የወሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት አወል ሰይድ (ዶ/ር) ገለፁ።
የወሎ ዩኒቨርሲቲ በተለያየ መርሃ ግብር በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን 843 ተማሪዎች ዛሬ አስመርቋል።

የወሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት አወል ሰይድ (ዶ/ር)፤ ምሩቃን ተማሪዎች የተለያዩ ውጣ ውረዶችን አልፈው ለዛሬ ምርቃት በመብቃታቸው እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።
በቆይታቸው ያገኙትን እውቀት፣ ልምድና ክህሎት ተጠቅመው ሀገርና ህዝባቸውን በእኩልነት፣ በታማኝነትና በቅንነት ሊያገለግሉ ይገባል ብለዋል።
ምሩቃን ስራ ፈጣሪ እንጅ ስራ ፈላጊ እንዳይሆኑ ያሳሰቡት ፕሬዚዳንቱ፣ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ተጠቅመው በተለያዩ ዘርፎች ስራ ሊፈጥሩና ኢኮኖሚውን ሊደግፉ ይገባል ብለዋል።
በሚሄዱበት አካባቢና በሚያገኙት አጋጣሚ ሁሉ ለኢትዮጵያ አንድነትና ሰላም እንዲሰሩም አመልክተዋል።
የእለቱ የክብር እንግዳና የደሴ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ሽመልስ ጌታቸው በበኩላቸው፣ ምሩቃን በቆይታቸው ያገኙትን ልምድና ክህሎት ወደ ተግባር በመቀየር ህዝብና ሀገር ሊያገለግሉ ይገባል ብለዋል።

የዛሬው ምርቃት የድል መጀመሪያ እንጅ መጨረሻ አለመሆኑን ተረድተው በቀጣይም እውቀትና ክህሎታቸውን በማሳደግ ለዲጂታል ኢትዮጵያ ትግበራ ስኬት የድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።
ታላቅ ህልምና ራዕይ ሰንቀው፣ ስነ ምግባራቸውን ጠብቀው፣ በታማኝነት የህብረተሰብ አገልጋይ እንዲሆኑም መክረዋል።
ተመራቂዎች ችግርና ፈተናዎችንም ወደ እድል በመቀየር የጀመሩትን የስኬት ጉዞ ሊቀጥሉ እንደሚገባ አመልክተው የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በእንሰሳት ህክምና ተመራቂዎች መካከል ተመስገን አሊ በሰጠው አስተያየት፤ በቆይታው ያገኘውን እውቀትና ክህሎት ተጠቅሞ በታማኝነት ለማገልገል ዝግጁ መሆኑን ገልጿል።
በመርሃ ግብሩ ላይም የደሴ ከተማና የወሎ ዩኒቨርሲቲ አመራሮች፣ የተማሪ ወላጆችና ቤተሰቦችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026