የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በካፋ ዞን በዘንድሮ የመኸር እርሻ ከ126 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ይለማል

Jun 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ቦንጋ ፤ ሰኔ 19 /2018 (ኢዜአ)፦ በካፋ ዞን በዘንድሮ የመኸር አዝመራ ከ126 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት እንደሚለማ የዞኑ ግብርና መምሪያ ገለፀ።

የዞኑ ግብርና መምሪያ የ2018 ዓመተ ምህረት የግብርና ተግባራት አፈጻጸም ግምገማና የ2018/19 የመኸር ግብርና ስራዎች ዕቅድ ንቅናቄ መድረክ አካሄዷል።

በመድረኩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ ለግብርናው ዘርፍ የተሰጠውን ትኩረት በማጠናከር ምርትና ምርታማነትን ይበልጥ ለማሳደግ ርብርብ ይደረጋል ብለዋል።


ግብርና ሁሉን አቀፍ ለውጥ ለማስመዝገብ ወሳኝ ዘርፍ በመሆኑ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግና ዘመናዊ አሰራሮችን በመከተል ያለውን አቅም አስተባብሮ ወደ ስራ በመግባት የአርሶና አርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት ማሳደግ ይገባል ብለዋል።

በዘንድሮው የመኸር እርሻ 126 ሺህ 491 ሄክታር መሬት ለማልማት መታቀዱን ገልፀዋል።

በዚህም የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት በየደረጃው በቁርጠኝነት ይሰራል ያሉት አስተዳዳሪው፣ ለአረንጓዴ አሻራ፣ ለቡና ልማትና ለአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ልዩ ትኩረት ይሰጣል ነው ያሉት።

የካፋ ዞን ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ህብረት ሥራ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ገረመው ገብሬ በበኩላቸው በዘንድሮው የመኸር እርሻ ከ3 ሚሊዮን 225 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።


ለዚህም የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን 40 በመቶ በማድረስና 30 በመቶ የሚሆነውን መሬት በክላስቴር በማልማት የታቀደውን ያህል ምርት ለማምረት ርብርብ ይደረጋል ብለዋል።

የግብዓት እጥረት እንዳይገጥም የተፈጥሮ ማዳበሪያ አጠቃቀም ላይ ትኩረት እንደሚሰጥ ያነሱት አቶ ገረመው የማይታረስ መሬትን ዜሮ በማድረስ የተያዘውን እቅድ ለማሳካት የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።

በዘንድሮው የመኸር አዝመራ የተያዘውን እቅድ ለማሳካት ቴክኖሎጂን ከመጠቀም ባለፈ ለኩታ ገጠም እርሻ ትኩረት በመስጠት ምርታማነትን ለማሳደግ እንደሚሰሩ የገለፁት ደግሞ የጠሎና ወረዳ ዋና አስተዳደሪ አቶ አትርሴ ሸታቸው እና የሺሾ እንዴ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ደምሴ ገብረማርያም ናቸው።

በ2017/18 የመኸር አዝመራ ከ123 ሺህ ሄክታር በላይ መሬትን በማልማት ከ2 ነጥብ 9 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡንም ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግባር ይጠናከራል-ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

ሚዛን አማን፣ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግ...

Jun 25, 2026

ፋውንዴሽኑ ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመቀናጀት ለስራ ፈጣሪ ወጣቶች ድጋፍ እያደረገ ነው

ጂንካ፤ሰኔ 15/2018(ኢዜአ) ፡-የኃይለማርያምና ሮማን ፋውንዴሽን ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመቀናጀት በሚያደርግላቸው ድጋፍ ተጠቃሚ መሆናቸውን በደቡብ ኦሞ እና...

Jun 23, 2026

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026