የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የደረጃ 'ለ' ግብር ከፋዮች ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል ሥርዓት ሊሸጋገሩ ነው

Jun 30, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ)፦ የደረጃ 'ለ' ግብር ከፋዮችን የሚያስተናግደው የ'eTax' ሥርዓት በ2019 ዓ.ም በጀት ዓመት ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል አገልግሎት አሰጣጥ እንደሚሸጋገር የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ።

የአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ቢሮ የሞደርናይዜሽን ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ መሃመድ አብዱረህማን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ ቢሮው ባለፉት ሁለት ዓመታት የአገልግሎት አሰጣጡን ውጤታማ ለማድረግ በርካታ የሪፎርም ሥራዎችን አከናውኗል።

በዚህም ግብር ከፋዮች በአካል ሳይመጡ በኢሜል እና በተዘረጋው የኦንላይን ሊንክ ብቻ አገልግሎቱን ማግኘት እንዲችሉ፣ ከገቢዎች ሚኒስቴር ጋር በመቀናጀት የተቀናጀ የልማት ሥርዓት ተዘርግቶ ወደ ተግባር መግባቱን አመልክተዋል።

ይህ አዲስ ዲጂታል አሠራር ግብር ከፋዮች ባሉበት ሆነው ምቹ አገልግሎት የሚያገኙበት ምኅዳር የፈጠረ ሲሆን፣ የባለቤትነት ስም ዝውውርን ጨምሮ የተለያዩ የሕግ ተገዥነት አገልግሎቶችንም በውስጡ ያካተተ መሆኑን ምክትል ቢሮ ኃላፊው አስረድተዋል።

ከዚህ በተጨማሪም ቢሮው በራሱ አቅም ያለማውን የዕዳ ክትትል ሥርዓት ወደ ተግባር በማስገባቱ፣በ17ቱም ቅርንጫፎች የሚወሰኑ የዕዳ ውሳኔዎችን በቅርበት ለመከታተልና የሚሰበሰበውን ገቢ በፍጥነት ወደ ካፒታል በመለወጥ ረገድ ከፍተኛ አፈጻጸም መመዝገቡን ነው የገለጹት።

የክሊራንስ (የግብር ነፃነቱ ማረጋገጫ) አሰጣጥ ሂደቱን ይበልጥ ግልጽ፣ ቀልጣፋና እምነት የሚጣልበት ለማድረግም ባርኮድ (Barcode) ያለው አዲስ የኦንላይን አሠራር ተግባራዊ መደረጉንም እንዲሁ።

የተዘረጉት እነዚህ የዲጂታል አገልግሎቶች ግብር ከፋዮች ባሉበት ሆነው ግብራቸውን እንዲያሳውቁና እንዲከፍሉ በማስቻላቸው፣ በየወሩ መጨረሻ ላይ በቅርንጫፍ ቢሮዎች ይታይ የነበረውን ከፍተኛ መጨናነቅና የረጅም ጊዜ ጥበቃ ሙሉ በሙሉ ማስቀረት መቻሉን አመልክተዋል።

ቢሮው በቀጣዩ በጀት ዓመትም የደረጃ "ለ" ግብር ከፋዮችን የሚያስተናግደውን የኢቲ ታክስ (eTax) ሥርዓት ሙሉ ለሙሉ ወደ ዲጂታል በማሸጋገር፣ ግብር ከፋዮች ካሉበት ሳይንቀሳቀሱ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችሉ ተጨማሪ ማሻሻያዎችን እንደሚተገብር ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የተጠናከረ የሰብል ጥበቃ ሥራ በቅንጅት እየተከናወነ ይገኛል

አዳማ ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀናጀ የሰብል ጥበቃ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ግብርና ...

Jun 29, 2026

በክልሉ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግባር ይጠናከራል-ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

ሚዛን አማን፣ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግ...

Jun 25, 2026

ፋውንዴሽኑ ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመቀናጀት ለስራ ፈጣሪ ወጣቶች ድጋፍ እያደረገ ነው

ጂንካ፤ሰኔ 15/2018(ኢዜአ) ፡-የኃይለማርያምና ሮማን ፋውንዴሽን ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመቀናጀት በሚያደርግላቸው ድጋፍ ተጠቃሚ መሆናቸውን በደቡብ ኦሞ እና...

Jun 23, 2026

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026