የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ፕሮጀክቱ የኢትዮጵያ ምርቶች በዓለም አቀፍ ገበያ ላይ ያላቸውን ተፈላጊነትና ተወዳዳሪነት ይበልጥ ለማሳደግ ትልቅ አቅም ይፈጥራል

Jun 30, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 22/2018 (ኢዜአ):-የብሔራዊ የንግድ ጥራት መሠረተ ልማት ማጠናከሪያ ፕሮጀክት የኢትዮጵያ ምርቶች በዓለም አቀፍ ገበያ ላይ ያላቸውን ተፈላጊነትና ተወዳዳሪነት ይበልጥ ለማሳደግ ትልቅ አቅም የሚፈጥር መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴዔታ እንዳለው መኮንን ገለጹ።

በኮሪያ ዓለም አቀፍ የልማት ትብብር ኤጀንሲ (KOICA) የሚደገፈውና የኢትዮጵያን ምርቶች በዓለም አቀፍ ገበያ ላይ ያላቸውን ተፈላጊነትና ተወዳዳሪነት ይበልጥ የሚያሳድገው "የብሔራዊ የንግድ ጥራት መሠረተ ልማት ማጠናከሪያ ፕሮጀክት" በዛሬው ዕለት በይፋ ተጀምሯል።


በፕሮጀክቱ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር)፣ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ድኤታ አቶ እንዳለው መኮንን፣ የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር መሠረት በቀለ (ዶ/ር) እና የኮይካ (KOICA) ምክትል ፕሬዚዳንት ሺን ስንግ ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ድኤታ አቶ እንዳለው መኮንን በዚሁ ወቅት፤ ፕሮጀክቱ በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት የሚተገበር መሆኑን ገልጸዋል።

ይህ የሀገሪቱን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ እንዲሁም የውጭ ንግድ ተወዳዳሪነትን በከፍተኛ ደረጃ ለማጠናከር ጉልህ ሚና እንደሚኖረው አስገንዝበዋል።

ፕሮጀክቱ የጥራት መሠረተ ልማት ተቋማትን አቅም በመገንባት የላብራቶሪ ምርመራና የደረጃዎች ዝግጅት ሥርዓትን ዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቀ እንዲሆን እንደሚያስችል ጠቁመዋል።

በዚህም የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶች በጥራት ለአገር ውስጥና ለውጭ ገበያ እንዲቀርቡ የቁጥጥርና የምርመራ አቅም ይጎለብታል ብለዋል።

አሰራሩ የአገር ውስጥ ምርቶች በዓለም አቀፍ ገበያ ተቀባይነት እንዲያገኙ ከማድረግ ባለፈ፣ ደረጃቸውን ያልጠበቁና ጥራታቸውን ያልጠበቁ ምርቶች በሀገር ውስጥ እንዳይሰራጩ ለመግታት እንደሚያግዝም አመላክተዋል።


የኮሪያ ዓለም አቀፍ የልማት ትብብር ኤጀንሲ (KOICA) ምክትል ፕሬዚዳንት ሺን ስንግ በበኩላቸው፤ የተመደበው ድጋፍ በዘርፉ የተሰማሩ የጥራት መሠረተ ልማት ባለሙያዎችን በዘመናዊ ቴክኖሎጂና አሠራር ለማሰልጠንና ብቃታቸውን ለማሳደግ የሚውል መሆኑን አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የተጠናከረ የሰብል ጥበቃ ሥራ በቅንጅት እየተከናወነ ይገኛል

አዳማ ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀናጀ የሰብል ጥበቃ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ግብርና ...

Jun 29, 2026

በክልሉ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግባር ይጠናከራል-ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

ሚዛን አማን፣ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግ...

Jun 25, 2026

ፋውንዴሽኑ ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመቀናጀት ለስራ ፈጣሪ ወጣቶች ድጋፍ እያደረገ ነው

ጂንካ፤ሰኔ 15/2018(ኢዜአ) ፡-የኃይለማርያምና ሮማን ፋውንዴሽን ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመቀናጀት በሚያደርግላቸው ድጋፍ ተጠቃሚ መሆናቸውን በደቡብ ኦሞ እና...

Jun 23, 2026

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026