የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ዩኒቨርሲቲው የተሻሻሉ የወተት ላም ዝርያዎችን በማራባት ለአካባቢው አርሶ አደሮች እያከፋፈለ ነው

Jul 1, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አምቦ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ የአምቦ ዩኒቨርሲቲ የተሻሻሉ የወተት ላሞች ዝርያ በማራባት የአካባቢው አርሶ አደሮች ተጠቃሚ እንዲሆን የበኩሉን ድጋፍ እያደረገ መሆኑን አስታወቀ።

በአምቦ ዩኒቨርሲቲ ጉደር ማሞ መዘመር ካምፓስ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ዳይሬክተር ዶክተር አማን ሪቂቱ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ተግባሩ ጎን ለጎን፣ በምርምር በማስደገፍ የተሻሻሉ የወተት ላሞችን በማራባት ለአካባቢው አርሶ አደሮች እንዲደርሱ እያደረገ ነው።

ዩኒቨርሲቲው ከቶኬ ኩታዬ ወረዳ ጋር በመቀናጀት፣ ድጋፍ የሚገባቸውን የማኅበረሰብ ክፍሎች በመለየት የወተት ላሞቹ የሚቀርቡበትን ሁኔታ በማመቻቸት ድጋፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።

ይህም የአርሶ አደሮቹን ገቢ ከመጨመር ባለፈ፣ በአካባቢው የወተትና የወተት ተዋጽኦ በሰፊው ለገበያ እንዲቀርብ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ዩኒቨርሲቲው ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ እስካሁን ድረስ 15 ዝርያቸው የተሻሻለ የወተት ላሞች ለአካባቢው አርሶ አደሮች መስጠቱን ተናግረዋል።

በካምፓሱ የወተት ከብት እርባታ ምርምር ቡድን መሪ አቶ ተሬሳ ተመስገን በበኩላቸው፤ ዩኒቨርሲቲው የማህበረሰቡን የወተት ምርት ለማሳደግ የሆሮ፣ ቦረና እና የውጪ አገር ዝርያ ያላቸው ላሞች ዝርያን በምርምር በማዳቀልና በማራባት የአካባቢው አርሶ አደሮች እያከፋፈለ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በአሁኑ ወቅት በምርምር ዝርያቸው የተሻሻሉ 170 የወተት ላሞች እንደሚገኙ አንስተው፤ ከእነዚህም መካከል በዘንድሮው ዓመት 10 የሚሆኑትን ለአርሶ አደሮች ለማድረስ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

በምዕራብ ሸዋ ዞን የቶኬ ኩታዬ ወረዳ አርሶ አደር ምስጋና ለታ እንደተናገሩት፤ ከዩኒቨርሲቲው ከተሰጣቸው የወተት ላም በቀን እስከ 15 ሊትር ወተት እያገኙ ነው።

የወተት ምርቱን ለአካባቢው ሕብረተሰብ በማቅረብ በሚያገኙት ገቢ ቤተሰቦቻቸውን በጥሩ ሁኔታ እያስተዳደሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የተጠናከረ የሰብል ጥበቃ ሥራ በቅንጅት እየተከናወነ ይገኛል

አዳማ ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀናጀ የሰብል ጥበቃ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ግብርና ...

Jun 29, 2026

በክልሉ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግባር ይጠናከራል-ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

ሚዛን አማን፣ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግ...

Jun 25, 2026

ፋውንዴሽኑ ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመቀናጀት ለስራ ፈጣሪ ወጣቶች ድጋፍ እያደረገ ነው

ጂንካ፤ሰኔ 15/2018(ኢዜአ) ፡-የኃይለማርያምና ሮማን ፋውንዴሽን ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመቀናጀት በሚያደርግላቸው ድጋፍ ተጠቃሚ መሆናቸውን በደቡብ ኦሞ እና...

Jun 23, 2026

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026