የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ቡናን በጥራት በማምረት በዓመቱ የታቀደውን የውጭ ምንዛሪ ግኝት ለማሳካት ርብርብ እየተደረገ ነው

Jul 1, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሃዋሳ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ ቡናን በጥራት በማምረት በዓመቱ የታቀደውን የውጭ ምንዛሪ ግኝት ለማሳካት ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታወቀ፡፡

ኢትዮጵያ ከቡና ገዢ ደንበኞቿ በተጨማሪ ከ20 በላይ አዳዲስ የዓለም ገበያዎችን መቀላቀሏ ይታወቃል።

ከኢትዮጵያ ቡና በዋነኝነት በመግዛት ቻይና የምትጠቀስ ሲሆን ካለፈው ዓመት በፊት የኢትዮጵያ ቡናን በመግዛት ከነበረችበት 33ኛ ደረጃ ተስፈንጥራ በአሁኑ ወቅት 4ተኛዋ ቡና ገዢ ሀገር ሆናለች።

ባለፈው ዓመት ብቻ ኢትዮጵያ ወደ ቻይና ከ35 ሺህ ቶን በላይ ቡና መላኳን መረጃዎች ያሳያሉ።

የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለፁት፤ በቡና ዘርፍ ለውጥ የሚያመጡ አዳዲስ ስትራቴጂዎች ተቀርጸው በተሰራው ስራ ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ ነው፡፡

በዚህም በየዓመቱ ለአለም ገበያ የሚቀርበውን የቡና ምርትና ጥራት በመጨመር ገቢውን ማሳደግ እንደተቻለ ተናግረዋል፡፡

በተያዘው 2018 በጀት ዓመትም ከ600 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለአለም ገበያ በማቅረብ 3 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት ግብ ተይዞ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

ዘንድሮ የአለም የቡና ዋጋ 40 በመቶ መቀነሱን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ በዓመቱ የተያዘውን የውጭ ምንዛሪ ግኝት ለማሳካት ጥራትን መሰረት ያደረገ ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

እስካሁንም ከ400 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለአለም ገበያ መቅረቡን ጠቅሰው በዓመቱ የተያዘውን እቅድ ለማሳካት የሚያስችል ምቹ ሁኔታ መኖሩን ገልጸዋል፡፡

በተለይም የውጭ ምንዛሪ ግኝትን ለማሳደግ የድህረ ምርት ጥራት አጠባበቅ ላይ በተሰራው ሰፊ ስራ በአለም ገበያ የኢትዮጵያ ቡና ተፈላጊነት መጨመሩን ተናግረዋል፡፡

የቡናን ጥራትና ምርታማነት የሚያሻሽሉ ቴክኖሎጂዎችን በመተግበርና በክልሎች ያሉ ተሞክሮዎችን በማስፋት በቀጣይም ዘርፉ በኢኮኖሚው ላይ እየተጫወተ ያለውን ሚና የማሳደግ ስራ በትኩረት እንደሚከናወን ገልጸዋል፡፡


የሲዳማ ክልል ቡና ፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መስፋን ቃሬ በበኩላቸው፤ በክልሉ በተያዘው በጀት ዓመት ከ26 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለማእከላዊ ገበያ ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

እስካሁን በተደረገ ጥረትም 24 ሺህ 100 ቶን ቡና ለማእከላዊ ገበያ መቅረቡን አስረድተዋል።

አለም አቀፍ የቡና ዋጋ መቀነስና ሌሎች ጉዳዮችን በምክንያት አንስተው እንደ ሃገር በጥራት በመወዳደር በእቅዱ የተያዘውን ግብ ለማሳካት እየተሰራ ነው ብለዋል።

በቀጣይም የቡና ጥራት ማሻሻያ ፓኬጆች አተገባበርን በማጠናከር የቡና ጥራትና ምርታማነትን የማሳደግ ተግባር በትኩረት እንደሚከናወንም አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የተጠናከረ የሰብል ጥበቃ ሥራ በቅንጅት እየተከናወነ ይገኛል

አዳማ ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀናጀ የሰብል ጥበቃ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ግብርና ...

Jun 29, 2026

በክልሉ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግባር ይጠናከራል-ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

ሚዛን አማን፣ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግ...

Jun 25, 2026

ፋውንዴሽኑ ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመቀናጀት ለስራ ፈጣሪ ወጣቶች ድጋፍ እያደረገ ነው

ጂንካ፤ሰኔ 15/2018(ኢዜአ) ፡-የኃይለማርያምና ሮማን ፋውንዴሽን ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመቀናጀት በሚያደርግላቸው ድጋፍ ተጠቃሚ መሆናቸውን በደቡብ ኦሞ እና...

Jun 23, 2026

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026