የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ቡናን በጥራት በማምረት በዓመቱ የታቀደውን የውጭ ምንዛሪ ግኝት ለማሳካት ርብርብ እየተደረገ ነው

Jul 1, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሃዋሳ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ ቡናን በጥራት በማምረት በዓመቱ የታቀደውን የውጭ ምንዛሪ ግኝት ለማሳካት ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታወቀ፡፡

ኢትዮጵያ ከቡና ገዢ ደንበኞቿ በተጨማሪ ከ20 በላይ አዳዲስ የዓለም ገበያዎችን መቀላቀሏ ይታወቃል።

ከኢትዮጵያ ቡና በዋነኝነት በመግዛት ቻይና የምትጠቀስ ሲሆን ካለፈው ዓመት በፊት የኢትዮጵያ ቡናን በመግዛት ከነበረችበት 33ኛ ደረጃ ተስፈንጥራ በአሁኑ ወቅት 4ተኛዋ ቡና ገዢ ሀገር ሆናለች።

ባለፈው ዓመት ብቻ ኢትዮጵያ ወደ ቻይና ከ35 ሺህ ቶን በላይ ቡና መላኳን መረጃዎች ያሳያሉ።

የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለፁት፤ በቡና ዘርፍ ለውጥ የሚያመጡ አዳዲስ ስትራቴጂዎች ተቀርጸው በተሰራው ስራ ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ ነው፡፡

በዚህም በየዓመቱ ለአለም ገበያ የሚቀርበውን የቡና ምርትና ጥራት በመጨመር ገቢውን ማሳደግ እንደተቻለ ተናግረዋል፡፡

በተያዘው 2018 በጀት ዓመትም ከ600 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለአለም ገበያ በማቅረብ 3 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት ግብ ተይዞ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

ዘንድሮ የአለም የቡና ዋጋ 40 በመቶ መቀነሱን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ በዓመቱ የተያዘውን የውጭ ምንዛሪ ግኝት ለማሳካት ጥራትን መሰረት ያደረገ ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

እስካሁንም ከ400 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለአለም ገበያ መቅረቡን ጠቅሰው በዓመቱ የተያዘውን እቅድ ለማሳካት የሚያስችል ምቹ ሁኔታ መኖሩን ገልጸዋል፡፡

በተለይም የውጭ ምንዛሪ ግኝትን ለማሳደግ የድህረ ምርት ጥራት አጠባበቅ ላይ በተሰራው ሰፊ ስራ በአለም ገበያ የኢትዮጵያ ቡና ተፈላጊነት መጨመሩን ተናግረዋል፡፡

የቡናን ጥራትና ምርታማነት የሚያሻሽሉ ቴክኖሎጂዎችን በመተግበርና በክልሎች ያሉ ተሞክሮዎችን በማስፋት በቀጣይም ዘርፉ በኢኮኖሚው ላይ እየተጫወተ ያለውን ሚና የማሳደግ ስራ በትኩረት እንደሚከናወን ገልጸዋል፡፡


የሲዳማ ክልል ቡና ፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መስፋን ቃሬ በበኩላቸው፤ በክልሉ በተያዘው በጀት ዓመት ከ26 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለማእከላዊ ገበያ ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

እስካሁን በተደረገ ጥረትም 24 ሺህ 100 ቶን ቡና ለማእከላዊ ገበያ መቅረቡን አስረድተዋል።

አለም አቀፍ የቡና ዋጋ መቀነስና ሌሎች ጉዳዮችን በምክንያት አንስተው እንደ ሃገር በጥራት በመወዳደር በእቅዱ የተያዘውን ግብ ለማሳካት እየተሰራ ነው ብለዋል።

በቀጣይም የቡና ጥራት ማሻሻያ ፓኬጆች አተገባበርን በማጠናከር የቡና ጥራትና ምርታማነትን የማሳደግ ተግባር በትኩረት እንደሚከናወንም አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026