🔇Unmute

ከቱሪዝም መሠረተ-ልማት ጋር በተያያዘ አበረታች ሥራዎች ተሠርተዋል። በተለይም በገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ስኬታማ ተግባራት ተከናውነዋል፤ አሁንም እየተከናወኑ ያሉና በቅርቡ የሚመረቁ አሉ።

ባለፉት ጥቂት ወራት ብቻ ኢትዮጵያ ውስጥ ሰባት የአውሮፕላን ማረፊያዎችን አስመርቀናል። በተጨማሪም በርካታ መንገዶች ተገንብተዋል። ይህም ለቱሪዝሙ ከፍተኛ መነቃቃት ይፈጥራል።

የኢትዮጵያ የግሉ ዘርፍ (ፕራይቬት ሴክተር) በገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች ግብ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ አሁን ለመጣው የቱሪዝም መነቃቃትና ሥራ የማይተካ ሚና ተጫውቷል።

ቱሪዝም ቅርስ ብቻ አይደለም፤ ቅርስ ስላለ በቀጥታ ቱሪዝም ይሳባል ማለት አይደለም። ቱሪዝም የተፈጥሮ ሀብት ብቻም አይደለም። ቱሪዝም ሸመታ ከሌለው በሴክተሩ የገንዘብ ልውውጦች (ትራንዛክሽን) ከሌለው የቱሪዝም ኢኮኖሚ ሊባል አይችልም።

ቱሪዝም በአጭሩ ሊጎበኘን የመጣ ሰው ልቡ ተደስቶ፤ ኪሱ ተራቁቶ መሄድ አለበት ማለት ነው።

ከፕሮሞሽን አንጻር ብዙ ሥራ ይጠበቅብናል። ብዙ የማስተዋወቅ ሥራ እንደሚቀረን እኛም እናውቃለን፤ ወዳጆቻችንም ይነግሩናል። እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ኢትዮጵያን አስውቦ፣ አሳምሮ፣ አልቆ የመሥራት ብቻ ሳይሆን የመግለጥ ኃላፊነት አለበት። ሀገራችንን ማስተዋወቁን በተቀናጀ መንገድ ስንሠራ የምናገኘውም ጥቅም በዚያው ልክ እያደገ ይሄዳል።

በሚሠሩት ሥራዎች የኢትዮጵያ ሕዝብ ቅርስ ይጠፋብኛል ብሎ ይሰጋል ብዬ አላምንም። እንደዛ ዓይነት ስጋት አላይም።

በዚህ ዓመት 10 ነጥብ 2 ጂ ዲ ፒ ዕድገት እንጠብቃለን። ይህ ዕድገት በኢትዮጵያ ብቻ እንጅ በድፍን አፍሪካ የለም።

በዚህ ዓመት ከ10 ነጥብ 8 እስከ 11 ቢሊየን ዶላር ኤክስፖርት እናደርጋለን። ይህ ከሁለት/ሦስት ዓመት በፊት ሦስት ቢሊየን ዶላር የነበረ ነው።

በዚህ ዓመት ከ1 ነጥብ 4 ሚሊየን በላይ የውጭ ሀገር ጎብኚዎች ኢትዮጵያን ጎብኚተዋል። ይህ ቁጥር ከካች አምናው አንጻር የ300 ሺህ እንዲሁም ካለፈው ዓመት አንጻር የ100 ሺህ ቱሪስቶች ቁጥር ጭማሪ አለው። ከውጭ ሀገራት ጎብኚዎችም (ማይንስ ተጨምሮ) ዘንድሮ ከ 5 ነጥብ 4 ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል።

በተመሳሳይ 50 ነጥብ 16 ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ደግሞ የተለያዩ የሀገራቸውን ክፍል ጎብኝተዋል። ይህ አሃዝ ከታች ዓምናው አንጻር በ9 ነጥብ 4 ሚሊየን እንዲሁም ካለፈው ዓመት አንጻር በ1 ነጥብ 8 ሚሊየን ብልጫ አለው።

ከሀገር ውስጥ ጎብኚዎች ከ79 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ተገኝቷል።

በዚህ ዓመት 204 ዓለም አቀፍ ኮንፈረንሶች ተካሂደዋል። ይህ አሃዝ ካለፈው ዓመት አንጻር የ50 ኮንፈረንሶች ብልጫ አለው። ከካች አምና አንጻር የ166 ኮንፈረንሶች ብልጫ አለው።

በዚህ ዓመት ለማይንስ (ኮንፈረንስ) ቱሪዝም ብቻ ከ166 ሺህ በላይ ተሳታፊዎች ወደ ኢትዮጵያ መጥተዋል።

ኢትዮጵያ በዚህ ዓመት 1 ነጥብ 5 ትሪሊየን ብር ትሰበስባለች። ከለውጡ በፊት 200/300 ሺህ ብር ነበር ዓመታዊ ገቢ የመሰብሰብ ዐቅም።
አዳማ ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀናጀ የሰብል ጥበቃ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ግብርና ...
Jun 29, 2026
ሚዛን አማን፣ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግ...
Jun 25, 2026
ጂንካ፤ሰኔ 15/2018(ኢዜአ) ፡-የኃይለማርያምና ሮማን ፋውንዴሽን ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመቀናጀት በሚያደርግላቸው ድጋፍ ተጠቃሚ መሆናቸውን በደቡብ ኦሞ እና...
Jun 23, 2026
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026