🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/ 2018 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ፈረንሳይ ሊዮን አዲስ የመንገደኞች በረራ ጀምሯል።
በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው፣ በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር አሌክሲስ ላሜክ እንዲሁም የአየር መንገዱ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ታድመዋል።
የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በረራው የሀገራቱን ግንኙነት የሚያጎለብት ነው።

በኢትዮጵያና በፈረንሳይ መካከል ያለውን የንግድ፣ ቱሪዝም እና የባህል ልውውጥ የሚያሳድግ መሆኑንም ጠቁመዋል።
አየር መንገዱ ወደ ፈረንሳይ ሊዮን የሚያደርገው በረራ በአውሮፓ 23ኛ መዳረሻው መሆኑን ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር አሌክሲስ ላሜክ በበኩላቸው፤ አየር መንገዱ ወደ ፈረንሳይ ሊዮን ያስጀመረው በረራ የሀገራቱን የንግድና ቱሪዝም ግንኙነት በማሳደግ ረገድ ትልቅ ምዕራፍ የሚከፍት መሆኑን ገልጸዋል።
ሊዮን የፈረንሳይ ሁለተኛዋ የኢኮኖሚ ማእከል መሆኗን ጠቅሰዋል።
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/ 2018 (ኢዜአ):- ኤጀንሲው ያስጀመረው የኦንላይን አገልግሎት የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባሉበት ሆነው በቀላሉ እንዲያገኙ ማስቻ...
Jul 3, 2026
አዳማ ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀናጀ የሰብል ጥበቃ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ግብርና ...
Jun 29, 2026
ሚዛን አማን፣ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግ...
Jun 25, 2026
ጂንካ፤ሰኔ 15/2018(ኢዜአ) ፡-የኃይለማርያምና ሮማን ፋውንዴሽን ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመቀናጀት በሚያደርግላቸው ድጋፍ ተጠቃሚ መሆናቸውን በደቡብ ኦሞ እና...
Jun 23, 2026